torsdag 18. august 2016

Democracy, Justice and Freedom for Ethiopian: በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለበጥ ግድ ነው!!

Democracy, Justice and Freedom for Ethiopian: በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለበጥ ግድ ነው!!:                     በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለበጥ ግድ ነው!!                                    ቃልኪዳን ካሳ...

በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለበጥ ግድ ነው!!

                    በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለበጥ ግድ ነው!! 

                                                                           ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ


በሀገራችን ኢትዮጵያ ከአራት ጊዜ ምርጫ ቢደረግም ያው እንደሚታወቀው ምርጫውን በማጭበርበር ስልጣኑ በሃይል ከተቆጣጠሩት ይህው ሁለት አስርት አመታትን አስቆጥሯል። ምርጫውን በሃይል ስልጣን መያዛቸውን እየታወቀ ለይመሰል የሚዘጋጁ ቅድመ ዝግጅቶችና የፓርቲዎች ተሳትፎ በጣም የሚያስገርም ነው። በአምባገነን ስርዓት የምትገዛ ሀገር የህዝቦችን ድምፅ ያከብራ ተብሎ አይገመትም። ለዚህም በህወሓት የሚመራው መንግስት ትልቁ ማሳያ ይሆናል።

ይህን ፁሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ነገር በሀገራቸን ውስጥ እየታየ ስላለው ህዝባዊ እንቢተኝነት ከጊዜ ወደ ጊዜ፣ ከቦታ ወደ ቦታ እንዲሁም ከከተማ ወደ ከተማ  በመላው ሀገሪቱ እየተስፋፋ መቷል። ይህ ህዝባዊ እንቢተኝነት በህወሓት ወገን የተለያዩ ስሞች ቢሰጠውም ህዝቡ የህወሓት አገዛዝ በቃን ብሎ የተነሳበት ወቅት ነው። ይህን ተከተሎ ባሳለፍናቸው ወራቶች ውስጥ በመላው ኦሮሚያ የተቀጣጠለው ህዝባዊ እንቢተኝነት እስካአሁን ድረስ አለ። የተዳፈነ ቢመስልም ረመጡ ግን ጊዜ እየጠበቀ መቀጣጠሉ የማይቀር ነው። በተመሳሳይ በወልቃይት የአማራ ማንነት ዙሪያ ላይ ውስጥ ውስጡን ሲቀጣጠል ቆይቶ ያልታሰበ እና ያልተጠበቀ የተቃውሞ የታየበት የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ በመላው አማራ ህዝብ የተነሳበት ተቃውሞ ነበር።

በሀገራችን ህወሓት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ በህዝቦቻችን ላይ እየፈፀመ ያለው ግፍና መከራ ጊዜውን ጠብቆ በእራሱ ጊዜና ሰዓት ገንፍሎ ወቷል። ጭቆናና በደል አልሸከምም ያለ ህዝብ ለነፃነቱ ህይወቱ መሰዋዓት እያደረገ ያለበት ሁኔታ ላይ ነው ያለነው። ህወሓቶች በሁሉም ብሄሮች ላይ ዘግንኛ የሆን ግፍና በደል ፈፅመዋል እየፈፀሙም ነው። ይህን ስል በአማራና በኦሮሞ እንዲሁም በጋምቤላ ህዝቦች የሰሯቸው ዘግናኝ ግፍና በደሎች ከሎሎች ብሄሮች ጋር እኩል ማድረጌ እንዳልሆን ትረዱኛላቹህ ብዬ ገምታለሁ። በአማራና በኦሮሞ ህዝብ ላይ የተፈፀመው በደል የአደባባይ ሚስጥር ነው። ህወሓቶች ሁለቱ ህዝቦች "ለስልጣኔ ያሰጉኛል" የሚል ትልቅ ስጋት አለው። ሌላኛው ሁለቱን ህዝብ በማናከስ ካልቻለ ደግሞ ከሁለት ህዝቦች የሚነሱ ጥያቄዎችን መልሳቸው ጥይት በማድረግ ተያይዞታል።

በህወሓት የሚመራው መንግስት መቶ ፐርሰንት መርጦናል ብለው ያስቡት ይሆን ባያስቡት ይሻላል። በህዝብ የተመረጠ ስርዓት ቢሆንማ ኖሮ ያ ሁሉ ህዝብ ባልተገደለ፣ ባልታሰረ፣ ባልታፈነ ነገሩ በህዝብ የተመረጡ ሳይሆን በጉልበትና በሃይል ስልጣን ላይ የተቀመጡ ስለሆን ለስልጣናችን ያሰጋናል የሚሉት ህዝብ ላይ እነሱ እንደሚሉት "የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን" እንዳሉት እያደረጉ ያለበት ሁኔታ ነው። ይህ ስርዓት የለየለት ሆኖል፤ ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ህዝብ ላይ እንዲህ ያለ አረመኔያዊ ድርጊት መፈፀሙ ምን ያህል የለየለት ስርዓት እንደሆነ አጉልቶ አሳይቶናል። በህወሓት የሚምራው መንግስት በህዝቦች ላይ ሁሉንም ነገር በአፈናና በመግደል ወይም በማሰር መፍትሄ የሚሆን መስሎቸው ህዝቡን ለመብቱና ለነፃነቱ እንዲቆም እያደረጉት እንደሆነ ልብ አላሉ። 

በዚህ ወቅት ህዝቡና በህወሓት የሚመራው መንግስት አይጥና ድመት ሁኔታ ውስጥ ተገብቷል። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ከዚህ በፊት ማንኛውም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሲታሰብ ፍቃድ በማለት ህብረተሰቡን ማጉላላት ነበር። አሁን ግን ህብረተሰቡ ከማስፈቀድ ማሰወቅ ብቻ ይጠበቅበናል በማለት የተለያዩ ህዝባዊ ሰልፎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። መብቱና ነፃነቱ ሲነጠቅ የነበረ ህብረተሰብ ከአሁን በኋላ ወይ ነፃነት ወይ ሞት ብሎ የተነሳ ህዝብ መሆኑ በተጨባጭ አሳይቷ። 

በህዝብ ያልተመረጠ በህዝብ ሊገለብጥ የግድ የሆነበት ምክንያት በህወሓት የሚመራው መንግስት በህዝቦች ላይ የሚፈፅሙት እየፈፀሙት ያለው ዘግናኝ ግፍና በደል ህዝቡን በማስቆጣት ሁሉም ለነፃነቱና ለመብቱ እንዲቆም አድርጎታል። በህዝብ ያልተመረጠ አምባገነናዊ ስርዓት ለህዝቦች ከመክራና ከስቃይ ያልዘለለ ምንም ሲያደርጉ አይስተዋሉም። ለዚህም በህወሓት የሚመራው መንግስት በኢትዮያዊያን ወገኖች ላይ የሚፈፅመውን ግድያም ሆን እስራት እንዲሁም አፈና አጥብቄ እቃወማለሁ። 



ድል ጭቁን ህዝብ!!
ውርደት ለአምባገኑ ህወሓት!!

tirsdag 24. mai 2016

ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ!

ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ!

ህወሃት 25 አመታት ሙሉ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ገንብቻለው እያለ መደስኮሩን ተያይዞታል። የህወሓት ገንብቻለው የሚለው ዲሞክራሲው ከወረቀትና ከአፍ ባልዘለለ መልኩ ሲነገርለት የሚኖረው ይህ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት አንድም ቀን በህዝቦች መካከል በስራ ላይ ሳይወል ይህው በወሬ ብቻ ሆኖ ቀረ።

ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር እንደታገሉ የሚነግሩን ህወሓቶች አንዲትም ቀን ለህዝቡ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት በተሞላበት መልኩ ለህዝቡም ሆን ለሀገሪቱ ሲሰሩ አይስተዋሉም። ከላይ እንደገለፅኩት የህወሓት ዲሞክራሲ ከወረቀትና ከአፍ ባልዘለለ መልኩ በምንም ላይ ሲተገበር አይታይም።

ዲሞክራሲ ማለት የመናገር መብት፣ የመፃፍ መበት፣  የመደራጀት መብት፣ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት እነዚህ ሁኔታ በሌሉበት እንዴት ነው ዲሞክራሲን በሀገሪቱ ላይ አምጥተናል ብለው መነገሩ። እውን ህወሓት ዲሞክራሲን እንዴት አድርጎ ቢተረጉመው ነው የታገልነው ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ነው ሲል። እርግጥ ነው በህወሓት ለህዝቡ የመታሰር፣ የመገደል፣ የመታፈን፣ የመሰደድ፣ የመፈናቀል፣ የመታፈን ስርዓት ገንብቷል ይህ የማይካድ ሀቀ ነው።

ዲሞክራሲ በሌለበት ሀገር ውስጥ ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተገንብቷል ብሎ ማሰቡ እጅግ ሞኝነት ነው። ዜጎች የመኖር ህልውናቸው አጣብቂኝ ውስጥ ባለበት ሀገር ውስጥ ዲሞክራሲ አለ ብሎ መናገሩ እራስን እያታለሉ መኖር ማለት ነው። ለህዝቡ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንደታገሉ ቢናገሩም ነገር ግን እነሱ የታገሉለት ዋነኛ አላማ የህዝቦችንና የሀገር ታሪክ ማጥፋትና የህዝቡን ሀብት ለመዝበር ነው። ህወሓት ስልጣኑን የያዘው በዲሞክራሲያዊ ስርዓት በህዝብ ተመርጦ የህዝብን ይሁንታ አግኝቶ የመጣ ስርዓት አይደለም፤ በሃይል ስልጣን ያዘ፤ በሃይል ሀገርና ህዝብን የገዛ ያለ ስርዓት ነው።


በእነዚህ ሁለት አስርት አመታት ውስጥ ህወሓት ክ፫ ያላነሱ ምርጫዎችን ቢያደርግም አንዱንም ጊዜ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አላደረገም። ይህ ባለበት ሁኔታ ላይ እለት ተዕለት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንደገነቡ ቢነግሩንም ሀቁ ግን በሀገሪቱና በህዝቦቹ ላይ የሚፈፀመው ኢፍት ሃዊ ድርጊቶች ሲፈፀሙና እየተፈፀሙ ያሉ ናቸው። ከ1997  ምርጫ ወዲህ በሀገሪቱ ላይ ምንም አይነት የዲሞክራሲ ባልታየበት ገነባነው ያሉትም ዲሞክራሲ ለዜጎች ፍትህ ሲያጓድል እንጂ ፍትህ ሲሰጥ አልተመለከትንም። የ1997 ዓም ምርጫ ተከትሎ ህወሓት ለስልጣኑ በመስጋት የተለያዩ አዋጆችን በማፅደቅ የመፃፍም ሆን የመናገር እንዲሁም የመደራጀት መብት እንዳይኖራቸው በማድረግ ህግ አውጥቶ አፅድቋል።

ይህን ተከትሎ ለዚሁ ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር ቀላል የሚባሉ አይደለም። በተለይ ፀረ ሽብር ህጉ አዋጅ ሆኖ ከፀደቀ ወዲህ ብዙን ምክንያትና አጋጣሚን እየጠበቁ ህዝቡን ለእስር እየተዳረጉ ይገኛል። ለዚህም ይህ አዋጅ ለሚፅፉ፣ ለሚደራጁ እንዲሁም ሀሳብን በነፃ ለሚገልፁ ለማፈን የወጣ ህግ ነው። ይህ ባለበት ሁኔታም ከህወሓት ጋር እየተናነቁ ያሉም ሀገርና ህዝብ ወዳድ ኢትዮጵያዊያን እጅግ የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው። ይህና መሰል ችግሮች ባለበት ሀገራችን ላይ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተገንብቷል ብሎ ከማለት "ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ" ቢባል ጥሩ ነው። ባይ ነኝ እኔ

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ

tirsdag 17. mai 2016

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ!
የዘንድሮን የግንቦት 20 በአል ስታከብሩ እነዚህ ስቃይና በደሎች ያሰባቹ መሆን አለበት። ግንቦት 20 የህዝብ በአል ነው ብሎ ማሰብ በህዝቡ ደምና በሞቱት ህይወት መቀለድ ነው።ህወሓት የስልጣን ዘመኑ ለማራዘም የገደለውን ገድሎ፣ያሰረውን አስሮ፣ያፈነውን አፍኖ ስልጣኑን በሃይል በመጠቀም ላይ ነው። ገና ከጅምሩ በጫካ በነበሩ ጊዜ ሲያቅዱ የነበረውን ነው አሁን እየፈፀሙ የሚገኙት ይህ ደግሞ እውነታ ከቀድሞ የህወሓት ሃላፊ የነበሩ አቶ ገ/መድህን አርያ የተናገሩት ሀቅ ነው።
Ginbot 20 Ferewoche
ይህን በአል ልታከብሩት የምትችሉት ህወሓቶችና ቤተሰቦቻችሁን እንዲሁም የትግራይ ካድሬዎች ብቻና ብቻ ነው። ይህን ያልኩበት ምክንያት ግልፅና ግልፅ ነው። በዚህ ስርዓት ውስጥ አብዛኛው ለትግራይ ተወላጆች ጥሩ እድል ፈጥሯል። ይህ የማይካድ ሀቅ ነው። ታዲያ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን የአንድ ብሄር ቢባል ምኑ ነው ውሽት!

የኢትዮጵያን ህዝብ በግንቦት 20 ያገኛው ድል ሳይሆን ውርደት ነው፤ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታ ነው። ስለግንቦት 20 ከድል ይልቅ ወርደቱ ጎልቶ የታየበት ወቅት ነው። እውነት በዚህ ወቅት በህወሓት በህዝቡ ላይ የሚፈፅመው ግፍና መከራ ተዘንግቶን ነው? በቅርቡ እንኳን በኦሮሚያ፣በአማራ በደቡብ ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ፣በኮንሶ፣በጋምቤላ ወገኖቻን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እንዲሁም ቀን በቀን የሚታሰረው ወገኖች እነዚህ ታዲያ የግንቦት 20 ፍሬዎች ቢባሉ ምን ይወጣላቸዋል።


ይሄን እውነታ ሁላችንም ጠንቅቀን እንረዳለን ዳሩ ግን ዝምታችን ወደር አቶ ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ክፉኛ ተለማመድ ነው መሰል ስምተንም ሆነ አይተን እኛ ግን እዛው የተቀመጥንበት ላይ ነን!!!!! ታዲያ የእኛ ተቃውሞ ምኑ ጋር ነው? መቃወም ብቻ ለውጥ አያመጣም፤እየተቃወምን ያለው ተደራጅተን ነው ወይስ እንዲሁ ነው? ሳንደራጅ፣ሳንሰባሰብ መቃወሙ ትርጉም አይኖረውም።
ስለዚህ እንሰባሰብ፣እንደራጅ፣እንመከከር . . . . . . . ከዛን ተቃውሟችን ለአንድ ህዝብ እስከሆነ ድረስ አሁን እየደረሰብን ያለውን ግፍና መከራ ከወሬ በዘለለ መልኩ ወደተግባር እንለውጠው።

ህወሓቶች ህዝብና ሀገር ለማጥፋት አንድ ሆነዋል። እኛ ሀገርና ህዝብን ለማዳን እንዴት እንድ መሆን አቃተን? ለነገሩ ለጥሩ ነገር ህብረት ሃይል የለውም፤ለመጥፎ ነገር ግን ህብረት ሃይል አለው። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወቅቱ የሚፈልገው ህብረትና አንድነት ነው። ይህን ህብረትና አንድነት ህወሓቶች ደግሞ አይፈልጉትም። ይህ ስርዓት በዚህ አይነት ከቀጠለ የህዝባችን ስቃይና መከራ እንደሚቀጥል እሙን ነው።

የግንቦት 20 ፍሬዎች መግደል፣መታሰር፣መታፈን፣መፈናቀል እንዲሁም መሰደድ ሲሆኑ በ25 አመታት ውስጥ እነዚሁ በህወሓት ሲተገበሩና እየተተገበሩ ያሉ ናቸው።


 የሁላችንም ችግር ህወሓትና ስርዓቱ ነው!



ፎቶዎችን በመሰብሰብና በማስተካከል የፌስቡክ ጓደኞቼ የረዱኝ ናትናኤል መኮንን እና ጥላዬ ታረቀኝ ከልብ አመሰግናለሁ።


የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የዘንድሮን የግንቦት 20 በአል ስታከብሩ እነዚህ ስቃይና በደሎች ያሰባቹ መሆን አለበት። ግንቦት 20 የህዝብ በአል ነው ብሎ ማሰብ በህዝቡ ደምና በሞቱት ህይወት መቀለድ ነው።ህወሓት የስልጣን ዘመኑ ለማራዘም የገደለውን ገድሎ፣ያሰረውን አስሮ፣ያፈነውን አፍኖ ስልጣኑን በሃይል በመጠቀም ላይ ነው። ገና ከጅምሩ በጫካ በነበሩ ጊዜ ሲያቅዱ የነበረውን ነው አሁን እየፈፀሙ የሚገኙት ይህ ደግሞ እውነታ ከቀድሞ የህወሓት ሃላፊ የነበሩ አቶ ገ/መድህን አርያ የተናገሩት ሀቅ ነው።

ይህን በአል ልታከብሩት የምትችሉት ህወሓቶችና ቤተሰቦቻችሁን እንዲሁም የትግራይ ካድሬዎች ብቻና ብቻ ነው። ይህን ያልኩበት ምክንያት ግልፅና ግልፅ ነው። በዚህ ስርዓት ውስጥ አብዛኛው ለትግራይ ተወላጆች ጥሩ እድል ፈጥሯል። ይህ የማይካድ ሀቅ ነው። ታዲያ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን የአንድ ብሄር ቢባል ምኑ ነው ውሽት!
የኢትዮጵያን ህዝብ በግንቦት 20 ያገኛው ድል ሳይሆን ውርደት ነው፤ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታ ነው። ስለግንቦት 20 ከድል ይልቅ ወርደቱ ጎልቶ የታየበት ወቅት ነው። እውነት በዚህ ወቅት በህወሓት በህዝቡ ላይ የሚፈፅመው ግፍና መከራ ተዘንግቶን ነው? በቅርቡ እንኳን በኦሮሚያ፣በአማራ በደቡብ ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ፣በኮንሶ፣በጋምቤላ ወገኖቻን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እንዲሁም ቀን በቀን የሚታሰረው ወገኖች እነዚህ ታዲያ የግንቦት 20 ፍሬዎች ቢባሉ ምን ይወጣላቸዋል።

ይሄን እውነታ ሁላችንም ጠንቅቀን እንረዳለን ዳሩ ግን ዝምታችን ወደር አቶ ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ክፉኛ ተለማመድ ነው መሰል ስምተንም ሆነ አይተን እኛ ግን እዛው የተቀመጥንበት ላይ ነን!!!!! ታዲያ የእኛ ተቃውሞ ምኑ ጋር ነው? መቃወም ብቻ ለውጥ አያመጣም፤እየተቃወምን ያለው ተደራጅተን ነው ወይስ እንዲሁ ነው? ሳንደራጅ፣ሳንሰባሰብ መቃወሙ ትርጉም አይኖረውም።
ስለዚህ እንሰባሰብ፣እንደራጅ፣እንመከከር . . . . . . . ከዛን ተቃውሟችን ለአንድ ህዝብ እስከሆነ ድረስ አሁን እየደረሰብን ያለውን ግፍና መከራ ከወሬ በዘለለ መልኩ ወደተግባር እንለውጠው።

ህወሓቶች ህዝብና ሀገር ለማጥፋት አንድ ሆነዋል። እኛ ሀገርና ህዝብን ለማዳን እንዴት እንድ መሆን አቃተን? ለነገሩ ለጥሩ ነገር ህብረት ሃይል የለውም፤ለመጥፎ ነገር ግን ህብረት ሃይል አለው። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወቅቱ የሚፈልገው ህብረትና አንድነት ነው። ይህን ህብረትና አንድነት ህወሓቶች ደግሞ አይፈልጉትም። ይህ ስርዓት በዚህ አይነት ከቀጠለ የህዝባችን ስቃይና መከራ እንደሚቀጥል እሙን ነው።

የግንቦት 20 ፍሬዎች መግደል፣መታሰር፣መታፈን፣መፈናቀል እንዲሁም መሰደድ ሲሆኑ በ25  አመታት ውስጥ እነዚሁ በህወሓት ሲተገበሩና እየተተገበሩ ያሉ ናቸው።

ፎቶዎችን በመሰብሰብና በማስተካከል የፌስቡክ ጓደኞቼ የረዱኝ ናትናኤል መኮንን እና ጥላዬ ታረቀኝ ከልብ አመሰግናለሁ።

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ!

የሁላችንም ችግር ህወሓትና ስርዓቱ ነው!

tirsdag 26. april 2016

ኢሳት እንወያይ ፕሮግራም!!


በኢሳት እንወያይ ፕሮግራም ላይ እኔ ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ እና ሀና ለገሰ ከአውስትራሊያ እንዲሁም የእንወያይ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ጋዜጠኛ ደረጀ ሀብተወልድ ጋር በመሆን በሀገራችንና በህዝቦቻችን እየደረሰ ግፍና መከራ በተለይ በአሁን ወቅት በተለዩ ቦታዎች ህወሓት ሲፈፅምና እየፈፀመ ያለው ኢሰብዓዊ ድርጊት በመቃወም ተወያይተናል።

የዛሬው እንወያይ ፕሮግራም ከ10 ቀን በፊት በጋምቤላ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እጅግ ዘግናኝ እና አሰቃቂ እንደነበር ሁላችንም የተመለከትነው ጉዳይ ነው። በውይይታችን ውስጥ ከመንግሥት የተሰጠው የሀዘን መግለጫ፣በመከላከያ ሰራዊቱ በክልሉ በተደጋጋሚ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋዎች እንዳሉ እየታወቁ በመንግስት ለነዋሪዎቹ በቂ ጥበቃ እንዳላደረገላቸው እንዴት ድንበር ያለጠባቂዎች እንዲሆን ለምን ተደረገ፣ ታፍነው ስለተወሰዱ ህፃናት እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ምን ይመስላል፣ከዚህ ጭፍጨፋ በስተጀርባ የህወሓት እጅ እንዳለበት እንዲሁም ጊዜውን ያልጠበቀ የሀዘን ቀን መታወጁ በተጨማሪ በሶሻል ሚዲያው ስለኢትዮጵያዊነት እጅግ በጣም ደስ እንደሚል እና ይህን በሶሻል ሚዲያ ላይ ያለውን አንድነት ወደ አንድ ነገር መደረስ እንዳለበት እና እነዚህና መሰል ችግሮችን በማንሳት ተወያይተናል።





søndag 27. mars 2016

ከብሄር በፊት ሀገር!!!

ከብሄር በፊት ሀገር!!!

በሀገራችና በህዝባችን ህወሓት ከሚፈፅማቸው ግፍና በደል በተጨማሪ በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ሁኔታ የብሄርተኝነትን መርዝ አሰራጭቶል እያሰራጨም ይገኛል። ይህንም ያደረገበት ዋነኛ ምክንያት የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ሆን ብሎ ያደረገው ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የራሱ የሆነ ብሄር እንዳለሁ ሁሉ ሰው ብሄርተኝነቱን እራሱ ፈልጎት የመጣ ነገር አይደለም፤ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ነው። ስለዚህ ህወሓት አሁን ላይ ስልጣኑን ለማራዘም ብሎ ብሄርን ከብሄር ማናከስ ትልቁ ስራው አድርጎታል፤ እያናከሰም ይገኛል። እስከመቼ በብሄር ፖለቲካ እያጫወተን እንዘልቀዋልን። ህወሓት ገና ጫካ እያለ አላማ አድርጎ የተነሳው የህዝቦችን አንድነት የመበጣጠስ አላማ አድርጎ የተነሳ ቡድን ነው።

አሁን ላይ በሀገራችን ያለው ስልጣን የአንድ ብሄር ስልጣን ነው። ይህ የአንድ ብሄር ስልጣን ለ25 አመታት በኢትዮጵያና በህዝቦቾ ታሪክ ግፍና በደል እንዲፈፀም አድርጓል። ህወሓት ብሄር ተደራጅቶ በሀገርና በህዝብ ላይ ይህ ነው የማይባል ኢፍትሃዊ ግፍና በደል ፈፅሟል፤ እየፈፀመም ይገኛል። መቼም አሁን አሁን እየተፈፀመ ያለው ግፍና በደል በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ይህም የሆነበት ምክንያት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በዜጎች ላይ የተወሰደው እኩይ ተግባር ይህ ነው የሚባል አይደለም።

የአንድ ብሄር ስልጣን ላይ መቀመጥ በዜጎች ላይ የሚደርሱ ግፍና በደሎች ሰሚ አካል የላቸውም። ምክንያቱም ሀገሪቱና ህዝቦቾን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አድርገውታል። ህግ አውጪ እነሱ፣ ህግ ተርጓሚ እነሱ፣ ህግ አስፈፃሚ እነሱ ይህ ሁኔታ ባለበት ሀገር ላይ የዜጎች የመኖር ዋስትና አጣብቂኝ ውስጥ ይገኛሉ። ይህን የፈጠረው የአንድ ብሄር ስልጣን ስለሆነ በህዝባቸው የሚፈፀምባቸውን በደል ወይም ግፍ ለመቃወም የብሄር ትግል እንዲያስቡ ያስገድዳቸዋል። ነገር ግን የብሄር ትግሉ መደረጉ ባይጠላም፤ ሀገራዊ ትግል እንዲሆን መፈጠሩ ሁሉምንም ብሄር ያካተተ ያደርገዋል።

ህወሓት ሲታገል የነበርው አንድን ብሄር ነፃ ለማውጣት ታግሎ፤ አንድን ብሄር ለስልጣን አብቅቷል። ይህ ስርዓት አብዛኛውን ብሄር ብሄረሰብ  ጎድቶታል እየጎዳውም ነው። አንዳንቺን ለአንዳንቺን እንዳንያያዝ፣ እንዳንግባባ፣ እንዳንሰማማ፣ እንዳንተማመን…………….. ያደረገ ስርዓት ነው። የአንድ ብሄር ስልጣን የፈጠርውን ችግር እያየን የብሄር ትግል ውስጥ የገባን ልብ ብለን ልንገነዘብ ይገባናል። "አንድ ተረት አለ እሳትን ያየ በአመድ አይስቅም!!"

ኢትዮጵያ የብዙ ብሄር ብሄረሰቦች ሀገር ናት። እያንዳንዱ ብሄር ብሄረሰብ የራሱ የሆን ቋንቋና ባህል ወግ አለው። ለዘመናት ተከባብሮና ተፋቅሮ የኖረ ማህበረሰብ ነው። አሁን አሁን ህወሓት በፈጠረው ስርዓት ብሄር ከብሄር ጋር ሲያስማማ ወይም ሲያከባብር አልተስተዋለም። ይህም የሆነበት ዋነኛ ምክንያት በሀገሪቱ የአንድ ብሄር ስልጣን ዘመን እንዲራዘም ሆን ተብሎ የሚደረግ ድርጊት ነው።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በዚህ ሶሻል ሚዲያ ላይ የሚስተዋሉ ነገሮች አሉ። እነዚሁ ነገሮች ብሄር እና ሀገር እየታገልን ያለነው ስለብሄር ነው ወይስ ስለሀገር የሚለውን ነገር እንድመለከት አድርጎኛል። ሁላችንም የእኔ የምንለው ብሄር አለን። እንዱሁም ሁላችንም በአንድ ስም ሊያስጠራን የሚችል ሀገርም አለን!! ታዲያ ትግላችን ከሀገር ወደ ብሄር እየሄደ ይመስላል።  አንድ ብሄር ብቻውን ህወሓት ተቃውሞ ከስልጣን ያስወግዳል የሚል እምነት የለኝም። ባይሆን ሁሉም በተቃውሞ ቢሳተፍ አንድ ደረጃ ላይ እንደርስ ነበር። እርግጥ ነው በብሄራችን ላይ የሚፈፀሙ ግፍና በደሎች ስለብሄራችን እንድንቆም ያደርጉናል። በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ተቃውሞ የለኝም። ነገር ግን እየሆነ ያለው ሁሉም   ስለእራሱ ብሄሩ የሚታገል ከሆነ ስለሀገራዊ ትግል እንዴት ልናስብ እንችላለን። እዚህ ጋር ቆም ብለን እናስብ!!  

ከብሄር በፊት ሀገር!! ሀገር እየፈረሰ ብሄር ይኖራል ማለት ዘበት ነው!! ይህ ደግሞ ማንም ሰው ሊያውቀውና ሊገነዘበው ግድ ይላል። ሀገርን ውስጥ ብዙ ህዝቦች አሉ!! አሁን ላይ ህወሓት ሀገርና ህዝብ እያጠፋ የሚገኝበት ሰዓት ላይ ነን ፤ይህ ደግሞ ከማንም የተደበቀ አይደለም። እርግጥ ነው ህወሓትና ቤተሰቦቻቸው ይህን እውነታ አይቀበሉትም። ምክንያቱ አላማ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ያሉት በሀገሪቱ ህዝብ ንብረትና ሀብት ላይ ስለሆን በህወሓት ላይ ምንም አይነት ተቃውሞ መስማትም ሆን ማየት አይፈልጉም።

ስለሆነም የምናደርገው ትግል ሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦች  ያማከለ መሆን አለበት ለጋምቤላው ህዝብ ኦሮሞው ካልጮህለት፣ ለኮንሶ ህዝብ አማራው ካልጮህለት፣ ለሀረሪ ህዝብ ትግሬው ካልጮህለት. . . . . . . . ጩህታችን ለመላው ለህዝባችን ካላደረግነው ተመልሶ እንደ ህወሓት አይነት ስርዓት መገንባቱ የማይቀር ነው።  ህወሓት ግፍና በደል መላው ህዝባችን ላይ ነው። ድምፅ ለሌላቸው ህዝቦች ድምፅ መሆን ካልቻልን አሁንም ይህ ፋሺስት ስርዓት በሀገሪቱና በህዝቡ ላይ የሚያደረሰውን መከራ ይቀጥላል። ይህ እንዳይሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከብሄር በፊት ለሀገሩና ለመላው ህዝብ  መቆም አለበት!! ሀገር ሲኖር ብሄር ይኖራል። አንድ ብሄር ሀገር መሆን አይችልም!! ሀገር ግን የብዙ ብሄር ብሄረሰብ ናት!!



እግዚሐብሄር ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ይባርክ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!


ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

tirsdag 22. mars 2016

የህወሓት አገዛዝ መቃወም ሀገር መጥላት አይደለም!!

                               የህወሓት አገዛዝ መቃወም ሀገር መጥላት አይደለም!!

ለዚህ ፅሁፍ መነሻ ያደረኩት ነገር ቢኖር በስርዓቱ ደጋፊዎች ዘንድ የተለያዩ አስተያየቶች ይሰነዘራሉ። ከሚሰነዝሯቸው ሀሳቦች በተደጋጋሚ የምመለከትው ነገር ቢኖሮ የህወሓት አገዛዙ መቃወም ማለት ሀገር መጥላት አድርገው ሲገነዘቡ አስተውያለው።

በመጀመሪያ ደረጃ ህወሓትና ሀገር ይለያሉ!! ህወሓት ማለት የአንድ ብሄር ስብስብ ሲሆን፤ በትጥቅ ትግል ታግሎ ስልጣን የያዘ አንድ ቡድን ነው። ሀገር ማለት ብዙ ህዝቦችን፣ ብዙ ቋንቋዎችን፣ ብዙ ብሄሮችን፣ ብዙ ጎሳዎችን፣ ብዙ ባህሎችን፣ ብዙ እሴት. . . . . . . . . . ይዛ የምትኖር ማለት ነው። ከልዩነታቸው ተነስተን ብዙ ነገር ልንገነዘብ እንችላለን። እርግጥ ነው ይህ ሊናገሩ የሚችሉት ከአንድ አቅጣጫ ብቻ ነው። አንድ አባባል አለ “አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል” አይደል የሚባለው። ህወሓት ተቃውሞ ሲገጥመው ጥቅማቸው የሚነካባቸው አካላት አሉ፤ ለዚህም ነው ስርዓቱን ለሚቃወሙ ሰዎች ሀገራቸውን እንደሚጠሉ ተደርጎ የሚታዩት።

የህወሓት አገዛዙን መቃወም ሀገር መጥላት ጋር የሚያገናኛቸው ምንም ነገር የለም። ህወሓት በሀገሪቱና በህዝቦቾ ላይ የሚፈፅመውን እኩይ ተግባር መቃወም ከሀገር መጥላት ጋር ሊያገናኙ የማይችሉ ነገሮች ናቸው። ህወሓት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ እስከአሁን ድረስ በዜጎች ላይ የሚደረሰው ስቃይና መከራ ቀጥሏል። በመከራና ስቃይ ውስጥ ሆነው ሲቃወሙ እጣ ፈንታቸው ሞት ወይ እስራት በሆነበት ስርዓት ውስጥ ህወሓትም ሆን ደጋፊዎች ስርዓቱን መቃወም ሀገር እንደመጥላት ይመለከቱታል።

ሀገር መጥላት ለሚባለው ነገር፤ ማንኛውም ሰው ስለሀገሩ ልዩ ፍቅርና ክብር አለው። ስለሀገሩ ክብርና ፍቅርም ብዙ መሰዋዓትነት የሚከፍል፤ እየከፈለም የኖረ ህዝብ ነው። በየትኛውም አለም ላይ ሀገሩን የሚጠላ ህብረተሰብ የለም። በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ስርዓት መወደድም ሆን መጠላትም በመንግስትና በህዝቦች መካከል ያለው ግንኙነት ይወስነዋል።  ወደ እኛ ሀገር ስንመጣ እንደ መንግስት ሆኖ ሀገሪቱን እየገዛት ያለው የአንድ አካባቢ ተዋላጆች ብቻ በመሆኑ በህዝቦች እና በገዥው ስርዓት መካከል በጣም ከፍትኛ ችግር ይገኛል።

አሁን ላይ ህወሓትን መቃወም ማለት ከህዝብና ከሀገር ጎን መቆም ማለት ነው። በዚህ ወቅት በመላው ሀገሪቱ የአገዛዝ ስርዓቱን በመቃወም ላይ ይገኛሉ። ይህ ተቃውሞ ስርዓቱ በፈጠረው ተፅዕኖ የመጣ ነው። በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ተቃውሞ ይበልጥ መጠናከሩ ሁኔታ በሀገሪቱ ላይ የመሬትን ወረራን በተመለከት ተቃውሞውን ይበልጥ አጎልቶታል። ህወሓትና ቤተሰቦቻቸው በአሁን ጊዜ በሀገሪቱ ላይ ከፈተኛ የመሬት ወረራ ላይ መጠመዳቸው ሁሉም ኢትዮጵያዊ የተገነዘበው ጉዳይ ነው።

ስለ ህወሓት ተቃውሞ በተመለከት ገና ከጅምሩ ሲታገል የነበረው አንድን ብሄር ነፃ ለማውጣትና የሀገሪቱን ታሪኳን ለማጥፋት ሲታገል የመጣ ቡድን ነው። ይህው በ25 አመታት ውስጥ በኢትዮጵያዊን ዜጎች በውጭም ሆን በሀገር ውስጥ የሚደርሱ አሰቃቂ ግፎች የዚህ ስርዓት ቅጥ ያጣ ስልጣን መከት ያደረገ መሆኑ ነው። እነዚህና ሌሎች ችግሮ በመመልከት ነው ተቃውሞ ከዕለት ወደ ዕለት ሊበረታ የቻለው።

ይህ ህዝብ ለስርዓቱን አልገዛም ማለቱ ሀገሩን እንደሚጠላ መታሰቡ የሚገርም ነው!! በህወሓት ዘመን ዳር ድንበር የተደፈረበት፣ ዜጎች የሚገደሉበት፣ የሚታሰሩበት፣ የሚሰደዱበት፣ የሚፈናቀሉበት ዘመን. . . . . . . ከዚህ ዘመን የተረፈን መከራና ውርደት ነው። ይህን መቃወም ሀገር መጥላት ሊባል አይገባም፤ ለሀገር ተቆርቋሪነት እንጂ እንሱ ይህን እኩይ ተግባር በሀገሪቱና በህዝቡ ላይ እየፈፀሙ ሀገር ጠሉ አልተባሉም።

ይህን አስመልክቶ ለሚነሱ ተቃውሞው በተለያዩ አጋጣሚዎች የተለያዩ ስም በካድሬዎችም ሆን በደጋፊዎቻቸው ሲሰጡ ይስተዋላል። ምንም አይነት ስም ቢሰጥም ህወሓትን ከመቃወም የሚሰንፍ የለም።


እግዚሐብሄር ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ይባርክ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

søndag 20. mars 2016

ህወሓትና የእምነት ተቋማት!!

ህወሓትና የእምነት ተቋማት!!

ከሌሎች ሀገራት እኛ ኢትዮጵያዊያን ለየት ከሚያደርጉን ነገሮች መካከል የሀይማኖት መቻቻል ነው።  በሀገራችን በኦርቶዶክስና በእስልምና ሃይማኖቶች መካከል ያለውን ለረዥም አመታት ተከባብሮና ተቻችለው የሚኖሩ  ሃይማኖቶች ናቸው። እነዚህ ሁለት የእምነት ተቋማት በእለት ተዕለት የአምልኮ ስርዓታቸው ዘወትር የሚከናውነው በራሳቸው የእምነት ስነ ስርዓት ነው። ይህ ደግሞ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የአምልኮ ስርዓት መሆኑ በሁሉም ዘንድ የሚታወቅ ነው።

አሁን አሁን በሀገራችን ውስጥ እየታየው ያለው ነገር ለማመን በሚቸግር መልኩ ነው። ይህን ያልኩበት ዋነኛ ምክንያት አንዳንድ የህወሓት ካድሬዎች በእምነት ተቋማት ውስጥ እየተዘወተሩ መተዋል። በተለይ በኦርቶዶክስ እምነት ተቋም ውስጥ መዘውተሩ እየተለመደ መቷል። ይህ አካሄድ በእጁጉ ልንቃወመው የሚገባ ነገር ነው። ቤተ እምነት ማለት እግዚሃብሄር የሚመለክበት እንደመሆኑ መጠን የመንግስት ስራ ማስፈፀሚያ ሲሆን ዝም ብሎ ማየቱ ተገቢ አይደለም።

ህወሓት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁለቱም በእምነት ተቋማት ውስጥ እየፈጠረ ያለውን ችግሮች ቀላል የሚባሉ አይደሉም። በሙስሊም እምነት ተከታዮች ላይ እየፈፀመ ያለው ግፍ ዝም ሊባል የሚገባ አይደለም። ስለሀይማኖታቸው ለሚቆሙ ሰዎች “አክራሪ” ወይም “አሸባሪ” የሚባል ስም ይሰጣቸዋል፤ ብሎም ለእስራት ይዳረጋሉ። ይህ ነገር እስከመቼ? በእንዲህ አይነቱ ይዘለቃል። ሌላኛው ደግሞ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሚስተዋሉ ችግሮች እየበዙ መተዋል፤ ለዚህም እንደማሳያ የምንመለከተው በማህበረ ቅዱሳን ላይ አዲስ ዘመቻ በመክፈት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የማስጠላት ስራ እየሰሩ መሆኑን ከማንም የተደበቀ አይደለም።

ይህ ሁኔታ በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ በሁለቱም የእምነት ተቋማት ውስጥ አሁን ከምናየውና ከምንሰማው ይበልጥ ችግሩ የከፋ ይሆናል። “ህወሓት በአሁን ሰዓት እጁ በጣም እረዝሟል።” በሁለቱ እምነት ተቋማት ላይ ካነጣጠር ጊዜያው ገፍቶል።

እያንዳንዳችን በየእምነታችን ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉትን የህወሓት ካድሬዎች ልንቃወም ይገባል። የእምነት ተቋማት ለህብረተሰቡ የአምልኮ አገልግሎት መስጫ እንጂ የመንግስት ፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ መሆን የለባቸውም። ህወሓት አሁን ላይ ታጥቆ የተነሳበት አላማ በየእምነት ተቋማቱ የራሱ የሆኑ ካድሬዎችን መልምሎ ለማስቀመጥ በሰፊው እየሰራበት ይገኛል። ስለዚህ ወገኖቼ የህወሓት መጠቀሚያ ከመሆን እንቆጠብ።
“ለየሀይማኖታችን ዘብ እንቁም!!”
እግዚሐብሄር ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ይባርክ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!



ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

lørdag 19. mars 2016

የፖለቲከኞችና የህሊና እስረኞች የአቋም ፅናት!!


የፖለቲከኞችና የህሊና እስረኞች የአቋም ፅናት!!

ህወሓት በስልጣን ዘመኑ በህዝቡ ላይ ብዙ እየፈፀማቸው ያለው ግፍ በዝቶል። በተለይ ከጥቂት አመታት ወዲህ የፀረ ሽብር ህጉን በማስታከክ በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚያደርሰው ግፍ ይህ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም።

ህወሓት ይህን የፀረ ሽብር አዋጅ ያረቀቀበት ዋንኛ ምክንያት የዜጎች በሚያደርጉት እንቅስቃሴዎች ሽብርተኛ ናቹ በማለት ለአገዛዙ እንዲመቸው አድርጎ ቀርፆታል። ይህ የሆነበት ዋንኛ ምክንያት የህወሓት አገዛዙን ለሚቃወሙ እንደማፈኛ ወይም እንደማስፈራሪያ የሚጠቀመው ህግ ነው።

ለዚህም ዜጎች ለዚህ አዋጅ ሰለባ የሆኑ እንዳሉ ሁላችንም የምናውቀው ነው። የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በዝተዋል። ለዚህም ዋንኛ ምክንያት አድርገው ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ተንቀሳቀሳቹሃል በማለት  ዜጎች ላይ ከ5 አመት እስክ እድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው ፍርደኞች ይገኛሉ። እነዚህ ፍርደኞች ያለምንም ማስረጃ በየማጎሪያ ቤቱ ይማቅቃሉ፣ ይሰቃያሉ ብሎም ለሞት ይዳረጋሉ። የእስራት ጊዜአቸውን ጨርሰው የውጡም ጥቂት ግለሰቦችም በእስር ቤቱ ይደርስባቸው የነበርውን እንግልት በጣም ዝግናኝ እንደሆን ሁላችንም እየሰማንና እያየን እንገኛለን።

እኔ አንድ የተደነኩበት ወይም ያስገረምኝ ነገር ቢኖር በእስር ላይ የሚገኙትም ሆን ከእስር የተለቀቁት እስረኞች አንድ አይነት አቋም አላቸው። በህወሓት እጅ ላይ ወድቆ እንዲህ ያለ የአላማ ፅናት በእጅጉ የሚያስደምም ነው። ይህ የአቋም ፅናት የመጣው እንዲሁ በከንቱ አይደለም፣ ዋጋ ተከፍሎበታል፣ እውነትን ይዘዋል፣ ስለህዝባቸው፣ ለሀገራቸው በእውነት ፀንተዋል። በህወሓት የሚደርስባቸውን ስቃይና መከራ ተቋቁመው በዛ መራር እስር ቤት ሆነው ለህዝቡ የሚሰጡት ተስፋ ከምንም በላይ ትልቅ ዋጋ አለው።

በመከራና ስቃይ ውስጥ ሆነ ስለህዝብ፣ ስለሀገር፣ ስለፍትህ፣ ስለመብት፣ ስለዲሞክራሲ ማሰቡ እጅግ የሚያስደንቅ ተግባር ነው። መቼም በዚህ ዘመን እንዲህ አይነቱን የአላማ ፅናት ለህወሓት እጅግ ከባድ ራስ ምታት ነው። እነዚህ ለነፃነት እና ለመብት መከበር ለሚታገሉ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ዘወትር ሊወደሱ ይገባቸዋል። እንደማናችንም ሰው ናቸው፤ ቤተሰብ አላቸው ናቸው!! እነሱ ከእኛ የሚለያቸው ስለሀገርና ስለህዝብ ዘወትር ፀንተው በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ነው።

የፀረ ሽብር አዋጁ እስካለ ድረስ ዜጎች በሚያደርጉት እለት ተዕለት እንቅስቃሴ አደጋ ውስጥ ነው። ይህ እንዲህ ባለበት ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በተጠናከረ መልኩ እንደቀጠለ ነው። ይህ የሆነበት ዋነኛ ምክንያት ለሁለት አስር አመታት የስርዓቱ የፈጠረው ትልቅ ተፅዕኖ መሆኖ ነው።


ሁላችንም በአቋማች እንፅና!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!

ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

fredag 11. mars 2016

ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም!!

ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም!!

እነዚህን እንስቶች መቼ በፌስቡክ መንደር ማየት ከጀመርን ሰንበት ብለናል። ስለነዚህ እንስቶችን ብዙ ማለት አልችልም። ምንም የማለት የሞራል አቅመም የለኝ። እንስቶች ለሀገራቸው እየከፈሉት ያለውን መሰዋትነት ቀላል የሚባል አይደለም።
እነሱ እንደ እኛ ሰው ናቸው። ያውም ሴት ወጣትነት የሚታይባቸው ሴቶች!! ሴትነት ሳይበግራቸው ከትግል ጎራ መቆማቸው በዚህ ዘመን ልዩና ልዩ ያደርጋቸዋል። እርግጠኛ ነኝ አጋንንሺው እንደማትሉኝ።
ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም። በተግባርም አሳይተዋል!! ደግሞሞ በ21 ክፍለ ዘመን ላይ ሆነው ያሳዩን ሴቶች ናቸው። በዚህ ዘመን ላይ እንዲህ ያሉ ሴቶችን ማግኝቱ እጅግ የሚደነቅ ነው።
እነዚህ እንስቶች እንደሰው ሁሉ ነገር የሚያምራቸው ናቸው። ማግባት፣ መውለድ፣ መማር፣ በቃ በዘመኑ ሴቶች የሚያደርጉትን ነገሮቹ ሁሉ ቢያደርጉ የማይጠሉ። ነገር ግን እነሱ ይህ የምንላቸውን ነገር በመተው ነው ትግል ጎራ መገኘታቸው ልናደንቃቸው ግንድ ይለናል።
የእነዚህ እንስቶች ፎቶዎች ባየዋቸው ቁጥር ብዙ ነገር ይሰማኛል። ይህን ስል በውስጣቸው ያለው ተስፋ አለመቁረጥ፣ የሀገር ፍቅር፣ የህዝብ ፍቅር፣ የሰንደቅአላማ ፍቅር......ኧረ ስንቱን!!
ክብር ለእነዚህ እንስቶች!!
ቃልኪዳን ካሳሁን

torsdag 10. mars 2016

በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!

በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!

ምን ብዬት መጀመር ግራ አገባኝ....... የቱን አንስቼ የቱን ልተው...... ምንስ ብፅፍ የውስጤን ቁጭት ይገልፀዋል......!! በህዝባችን ላይ እለት ተዕለት  እየተፈፀመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ እየሰማንና እያየን እስከመቼ.....በዝምታ እንኖራለን ግፉ ፅዋ ሞልቶ ፈሷል። ዜጎች በራሳቸው ሀገር፣ በራሳቸው መንደር፣ በራሳቸው ማንነት እንዳይኖሩ የሚደረግበት ሀገር ኢትዮጵያ!! 

ትናንት በኦሮሞና በጋምቤላው ወገናችን ላየ በደረሰው ኢሰብዓዊ ድርጊት ምን ያህልን ውስጣችን ስንቃጠል እንደከረምን ከሁላችን የማንረሳው ነው። ይባስ ዛሬ ደግሞ የገደሉትን ገለው፣ያሰሩትን አስረው ፣ይህ አለበቃ ሲላቸው የሰው ልጅ ከሰው ጋር አስሮ ማሰቃየት ላይ ደርሰዋል። ይህን እኩይ ተግባር ማየቱንም ሆን መስማቱ እንዴት እንዴት ያማል.....!! "በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!"

ስማኝ ልንገርህ ወገኔ ዛሬ ሱርማ ወገናች ላይ የተፈፀመው እኩይ ተግባር ነገ በእኔና በአንተ የገዛ ቤታችን ውስጥ መተው እንደሚያድርጉት አትጠራጠር። 21 ክፍለ ዘመን ላይ እየኖረን ኑሮቻች እና ስቃያችን 18 ክፍለ ዘመን ሆኖል። ይህን ግፍና ሰቆቆ እስከመቼ በዝምታ እንደምንገልፀው!!  

ጥቂቶች መብታቸውን ተከብሮ ነገር ግን ብዙሃኑ መብቱን እና ነፃነቱን ተነፍጎ የሚኖርባት ሀገር ኢትዮጵያ እየሆን ያለው በህዝባችን ላይ በእውነቱ ዝም የሚያስብል አይደለም። አሁን አሁንማ መብት ሲጠየቅ ምላሹ በመሳሪያ ሆኖል።  "በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!"

ይህን ግፍና መከራ እየሰማን፣ እየተመለከትን ስለምን ዝም አልን፣ ስለምን ዝምታን መረጥን፣ ስለምን በህዝባችን ላይ የሚደርሰውን ስቃይና መከራ ለማውገዝ አቅም አጣን፣ ስለምን የወገናችንን ሞት ሞታችን ማድረግ አቃተን፣ ስለምን መንገድ ዳር ስለሚገድሉብን ልጆች፣ እናቶች፣ ወጣቶች እንዲሁም አዛውንቶች እየሰማንና እያየን ዝምታን መረጥን!!

የእኛን ዝምታ እነሱን ካጀገነ ችግሩ እነሱ ጋር ሳይሆን እኛው ጋር ነው። ስለዚህ ስማኝ ልንገርህ ወገኔ ህወትን ከስልጣን ለማወረድ የእኛ ዝምታችን ሰባብረን በአንድነት ስንጮህ ነው። ተደራጅ፣ ተሰባሰብ፣ ተወያይ..........."የሀገር ጉዳይ ነውና" እንክፈል ጊዜችን፣ እንክፈል ገንዘባችን፣ እንክፈል ህይወታችን.........ነፃነት ዋጋ ታስከፍላለችና ያለ መሰዋትነት ድል የለምና መከፈል ላለበት መክፈል አለበት......... "ኢትዮጵያ ደምና አጥንት የተከፈለባት ሀገር ናት" አሁንም ልንከፍል ግድ ነው!! "በእኛ ዝምታ እነሱ ጀገኑ!!" 

በህዝቡ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የተቀጣጠለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በህዝባዊ እንቢተኝነቱን እንዲሳተፍ የየበኩላችን ጥረት እናድርግ ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ከዚህ ፋሽስት ስርዓት እንታደግ!!

"ህወሓት እስካለ ተቃውሞ አለ"

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!!
ድል ለጭቁኑ ህዝብ!!

ቃልኪዳን ካሳሁን   (ከኖርዌ)