søndag 20. mars 2016

ህወሓትና የእምነት ተቋማት!!

ህወሓትና የእምነት ተቋማት!!

ከሌሎች ሀገራት እኛ ኢትዮጵያዊያን ለየት ከሚያደርጉን ነገሮች መካከል የሀይማኖት መቻቻል ነው።  በሀገራችን በኦርቶዶክስና በእስልምና ሃይማኖቶች መካከል ያለውን ለረዥም አመታት ተከባብሮና ተቻችለው የሚኖሩ  ሃይማኖቶች ናቸው። እነዚህ ሁለት የእምነት ተቋማት በእለት ተዕለት የአምልኮ ስርዓታቸው ዘወትር የሚከናውነው በራሳቸው የእምነት ስነ ስርዓት ነው። ይህ ደግሞ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የአምልኮ ስርዓት መሆኑ በሁሉም ዘንድ የሚታወቅ ነው።

አሁን አሁን በሀገራችን ውስጥ እየታየው ያለው ነገር ለማመን በሚቸግር መልኩ ነው። ይህን ያልኩበት ዋነኛ ምክንያት አንዳንድ የህወሓት ካድሬዎች በእምነት ተቋማት ውስጥ እየተዘወተሩ መተዋል። በተለይ በኦርቶዶክስ እምነት ተቋም ውስጥ መዘውተሩ እየተለመደ መቷል። ይህ አካሄድ በእጁጉ ልንቃወመው የሚገባ ነገር ነው። ቤተ እምነት ማለት እግዚሃብሄር የሚመለክበት እንደመሆኑ መጠን የመንግስት ስራ ማስፈፀሚያ ሲሆን ዝም ብሎ ማየቱ ተገቢ አይደለም።

ህወሓት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁለቱም በእምነት ተቋማት ውስጥ እየፈጠረ ያለውን ችግሮች ቀላል የሚባሉ አይደሉም። በሙስሊም እምነት ተከታዮች ላይ እየፈፀመ ያለው ግፍ ዝም ሊባል የሚገባ አይደለም። ስለሀይማኖታቸው ለሚቆሙ ሰዎች “አክራሪ” ወይም “አሸባሪ” የሚባል ስም ይሰጣቸዋል፤ ብሎም ለእስራት ይዳረጋሉ። ይህ ነገር እስከመቼ? በእንዲህ አይነቱ ይዘለቃል። ሌላኛው ደግሞ በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሚስተዋሉ ችግሮች እየበዙ መተዋል፤ ለዚህም እንደማሳያ የምንመለከተው በማህበረ ቅዱሳን ላይ አዲስ ዘመቻ በመክፈት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የማስጠላት ስራ እየሰሩ መሆኑን ከማንም የተደበቀ አይደለም።

ይህ ሁኔታ በዚህ መልኩ የሚቀጥል ከሆነ በሁለቱም የእምነት ተቋማት ውስጥ አሁን ከምናየውና ከምንሰማው ይበልጥ ችግሩ የከፋ ይሆናል። “ህወሓት በአሁን ሰዓት እጁ በጣም እረዝሟል።” በሁለቱ እምነት ተቋማት ላይ ካነጣጠር ጊዜያው ገፍቶል።

እያንዳንዳችን በየእምነታችን ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉትን የህወሓት ካድሬዎች ልንቃወም ይገባል። የእምነት ተቋማት ለህብረተሰቡ የአምልኮ አገልግሎት መስጫ እንጂ የመንግስት ፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ መሆን የለባቸውም። ህወሓት አሁን ላይ ታጥቆ የተነሳበት አላማ በየእምነት ተቋማቱ የራሱ የሆኑ ካድሬዎችን መልምሎ ለማስቀመጥ በሰፊው እየሰራበት ይገኛል። ስለዚህ ወገኖቼ የህወሓት መጠቀሚያ ከመሆን እንቆጠብ።
“ለየሀይማኖታችን ዘብ እንቁም!!”
እግዚሐብሄር ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ይባርክ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!



ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar