fredag 11. mars 2016

ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም!!

ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም!!

እነዚህን እንስቶች መቼ በፌስቡክ መንደር ማየት ከጀመርን ሰንበት ብለናል። ስለነዚህ እንስቶችን ብዙ ማለት አልችልም። ምንም የማለት የሞራል አቅመም የለኝ። እንስቶች ለሀገራቸው እየከፈሉት ያለውን መሰዋትነት ቀላል የሚባል አይደለም።
እነሱ እንደ እኛ ሰው ናቸው። ያውም ሴት ወጣትነት የሚታይባቸው ሴቶች!! ሴትነት ሳይበግራቸው ከትግል ጎራ መቆማቸው በዚህ ዘመን ልዩና ልዩ ያደርጋቸዋል። እርግጠኛ ነኝ አጋንንሺው እንደማትሉኝ።
ሴት መሆን ምንም ከማድረግ የሚከለክል ነገር የለም። በተግባርም አሳይተዋል!! ደግሞሞ በ21 ክፍለ ዘመን ላይ ሆነው ያሳዩን ሴቶች ናቸው። በዚህ ዘመን ላይ እንዲህ ያሉ ሴቶችን ማግኝቱ እጅግ የሚደነቅ ነው።
እነዚህ እንስቶች እንደሰው ሁሉ ነገር የሚያምራቸው ናቸው። ማግባት፣ መውለድ፣ መማር፣ በቃ በዘመኑ ሴቶች የሚያደርጉትን ነገሮቹ ሁሉ ቢያደርጉ የማይጠሉ። ነገር ግን እነሱ ይህ የምንላቸውን ነገር በመተው ነው ትግል ጎራ መገኘታቸው ልናደንቃቸው ግንድ ይለናል።
የእነዚህ እንስቶች ፎቶዎች ባየዋቸው ቁጥር ብዙ ነገር ይሰማኛል። ይህን ስል በውስጣቸው ያለው ተስፋ አለመቁረጥ፣ የሀገር ፍቅር፣ የህዝብ ፍቅር፣ የሰንደቅአላማ ፍቅር......ኧረ ስንቱን!!
ክብር ለእነዚህ እንስቶች!!
ቃልኪዳን ካሳሁን

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar