lørdag 19. mars 2016

የፖለቲከኞችና የህሊና እስረኞች የአቋም ፅናት!!


የፖለቲከኞችና የህሊና እስረኞች የአቋም ፅናት!!

ህወሓት በስልጣን ዘመኑ በህዝቡ ላይ ብዙ እየፈፀማቸው ያለው ግፍ በዝቶል። በተለይ ከጥቂት አመታት ወዲህ የፀረ ሽብር ህጉን በማስታከክ በንፁሃን ዜጎች ላይ የሚያደርሰው ግፍ ይህ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም።

ህወሓት ይህን የፀረ ሽብር አዋጅ ያረቀቀበት ዋንኛ ምክንያት የዜጎች በሚያደርጉት እንቅስቃሴዎች ሽብርተኛ ናቹ በማለት ለአገዛዙ እንዲመቸው አድርጎ ቀርፆታል። ይህ የሆነበት ዋንኛ ምክንያት የህወሓት አገዛዙን ለሚቃወሙ እንደማፈኛ ወይም እንደማስፈራሪያ የሚጠቀመው ህግ ነው።

ለዚህም ዜጎች ለዚህ አዋጅ ሰለባ የሆኑ እንዳሉ ሁላችንም የምናውቀው ነው። የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በዝተዋል። ለዚህም ዋንኛ ምክንያት አድርገው ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ተንቀሳቀሳቹሃል በማለት  ዜጎች ላይ ከ5 አመት እስክ እድሜ ልክ እስራት የተፈረደባቸው ፍርደኞች ይገኛሉ። እነዚህ ፍርደኞች ያለምንም ማስረጃ በየማጎሪያ ቤቱ ይማቅቃሉ፣ ይሰቃያሉ ብሎም ለሞት ይዳረጋሉ። የእስራት ጊዜአቸውን ጨርሰው የውጡም ጥቂት ግለሰቦችም በእስር ቤቱ ይደርስባቸው የነበርውን እንግልት በጣም ዝግናኝ እንደሆን ሁላችንም እየሰማንና እያየን እንገኛለን።

እኔ አንድ የተደነኩበት ወይም ያስገረምኝ ነገር ቢኖር በእስር ላይ የሚገኙትም ሆን ከእስር የተለቀቁት እስረኞች አንድ አይነት አቋም አላቸው። በህወሓት እጅ ላይ ወድቆ እንዲህ ያለ የአላማ ፅናት በእጅጉ የሚያስደምም ነው። ይህ የአቋም ፅናት የመጣው እንዲሁ በከንቱ አይደለም፣ ዋጋ ተከፍሎበታል፣ እውነትን ይዘዋል፣ ስለህዝባቸው፣ ለሀገራቸው በእውነት ፀንተዋል። በህወሓት የሚደርስባቸውን ስቃይና መከራ ተቋቁመው በዛ መራር እስር ቤት ሆነው ለህዝቡ የሚሰጡት ተስፋ ከምንም በላይ ትልቅ ዋጋ አለው።

በመከራና ስቃይ ውስጥ ሆነ ስለህዝብ፣ ስለሀገር፣ ስለፍትህ፣ ስለመብት፣ ስለዲሞክራሲ ማሰቡ እጅግ የሚያስደንቅ ተግባር ነው። መቼም በዚህ ዘመን እንዲህ አይነቱን የአላማ ፅናት ለህወሓት እጅግ ከባድ ራስ ምታት ነው። እነዚህ ለነፃነት እና ለመብት መከበር ለሚታገሉ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ዘወትር ሊወደሱ ይገባቸዋል። እንደማናችንም ሰው ናቸው፤ ቤተሰብ አላቸው ናቸው!! እነሱ ከእኛ የሚለያቸው ስለሀገርና ስለህዝብ ዘወትር ፀንተው በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ነው።

የፀረ ሽብር አዋጁ እስካለ ድረስ ዜጎች በሚያደርጉት እለት ተዕለት እንቅስቃሴ አደጋ ውስጥ ነው። ይህ እንዲህ ባለበት ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በተጠናከረ መልኩ እንደቀጠለ ነው። ይህ የሆነበት ዋነኛ ምክንያት ለሁለት አስር አመታት የስርዓቱ የፈጠረው ትልቅ ተፅዕኖ መሆኖ ነው።


ሁላችንም በአቋማች እንፅና!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!

ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar