tirsdag 21. mai 2013

እናንት ወያኔዎች በጐጥ ያበዳቹህ፤


እናንት ወያኔዎች በጐጥ ያበዳቹህ፤
ዓርባ ዓመት የማይሽር የዘር ልክፍታቹህ፤
አጥንት የምትሰብሩ ደም ሥጋ ጠልቃቹህ፤
ስትወጉት ስትሰቅሉት ከአገሩ አሳዳቹህ፤
ታግሶ፤ ተማጽኖ ከጸብ ቢሸሻቹህ፤
የጥፋት ሰራዊት ባቢሎን ቀጥራቹህ፤
እንደ እባብ እራሱን አስቀጠቀጣቹህ፤
የሞት መቀጣጫ ዒላማ አድርጋቹህ፤
ዘር ፍጅት ዘመቻ በአማራ አውጃቹህ፤
ሞት በተገኘበት በአደን መንጥራቹህ፤
በአራቱም ማዕዘን አስጨፈጨፋቹህ፤
እናንት ጥቁር አይሁድ ትግሬም አይደላቹህ። 
እምነት ኃይማኖቱን ክብሩን አርክሳቹህ፤
የኤይድስ ደዌ በመርፌ ከትባቹህ፤
ትውልድ በሚሊዮን ዘር ያስጨረሳቹህ፤
በሃያ ዓመት በትር አላልቅ ቢላቹህ፤
በርሃብ ልትፈጁት ሜዳ በትናቹህ፤
ከቀየው ማሳደድ ሆኗል ዘመቻቹህ፤
ቤት ትዳሩን ማፍረስ በሞት ሽረታቹህ፤
ኦጋዴን፤ ማጆ ዞን፤ ቤሻንጉል አዛቹህ፤
በአገር በመዲናው ቤቱን አፍርሳቹህ፤
ሦስት ትውልድ አማራ ሜዳ በትናቹህ፤
ቀነኞች በምቾት እንቅልፍ ወሰዳቹህ፤
እናንት ጥቁር አይሁድ ትግሬም አይደላቹህ።
የጊዜ ሎተሪ ቀን በለስ ሰጥቷቹህ፤
በመስተዋት ቪላ ከፎቅ ከትማቹህ፤
ዘር ማንዝር መሰላል ሰገነት ወጥታቹህ፤
በሚሎዮን ሲቃ ድሎት ሸምታቹህ፤
በጥጋብ ዳንኪራ ባጥ የረገጣቹህ፤
መሰረት ግድግዳ አጥር አፍርሳቹህ፤
አገር ሕዝብ ሃይማኖት ታሪክ አጥፍታቹህ፤
በመሸበት ዘመን ቆጥ ሙጥኝ ብላቹህ፤
መበቃቀያችን ዋሻ አፈር ምሳቹህ፤
እንድንቀባበር ትገፉናችላቹህ፤
ቀን በሰቀላቹህ አንወርድም መስሏቹህ፤
ጽዋቹህ ተሞልቷል እንደየስፍራቹህ፤
እናንት ጥቁር አይሁድ ነግቷል ወዮላቹህ፤
ዛሬ ምሕረት ሻቱ ስለ አምላክ ብላቹህ። 

በኢትዮጵያ አራቱ ማዕዘን እየተሳደዱ የድረሱልንና የስቃይ ጥሪያቸውን 
እያሰሙ ለሚገኙት አማራ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ድጋፍ፤ አጋርነትና 
የትግል ጥሪ ትሁንልኝ። 

የጐንቻው! yegonchaw@yahoo.co.uk 

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar