torsdag 23. mai 2013

በጎንደር የሁለት ቀበሌ ወጣቶች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ


በጎንደር የሁለት ቀበሌ ወጣቶች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

ኢሳት ዜና:-የቀበሌ 6 እና  7 ወጣቶች ዛሬ ግንቦት14፣ 2005 ዓም ባደረጉት ሰልፍ የመብራት፣ የውሀ፣ የስራ አጥነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ጎንደር አደራጅና የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ሙላት ፍሰሀ ወጣቶቹ ብሶታቸውን ለመሳማት ለሰልፍ መውጣታቸውን ተናግረዋል።
በሰልፉ መጨረሻ ላይ አንዳንድ ወጣቶች በፖሊሶች ሲዋከቡ መታየታቸውን በስፍራው የተገኘው ተባባሪ ዘጋቢያችን ገልጿል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar