torsdag 14. november 2013



ዋና ጠላታችን የትግሬ ነፃ 
አውጪ ወያኔ ነው! 
ከቴዎደሮስ ሐይሌ 
‘’ ወዴት ነው የምንሄደው ለማን ነው 
የምንነግረው መንግስት ረስቶናል ኤንባሲው 
አላቃችሁም …ብሏል ነገ እኔ እህትህን ወይ ተደፍሬ 
ወይ ሞቼ ወይ አብጄ ነው የምታገኘኝ’’ አንዲት 
በሳውዲ ተደብቃ ያለች እህታችን ያስተላለፈችው 
መልዕክት 
አቦይ ስብሃት ከጉልምስና እስክ ሽምግልና የታገልክለት ኢትዮጽያና ኢትዮጽያዊነት የማዋረድ 
አላማህ ከሃገር አልፎ በአለም ሁሉ ሆኖዓልና እንኳን ደስ ያለህ አዜብ መስፍን የባልሽ እረፍት የለሹ እስከ 
መቃብር ያለመታከት የቆመለት አላማ ትቶት ያለፈው ራዕይ የአገዛዝ ውጤቱ ይህው ኢትዮጽያውያንን 
አንገት የማስደፋት ተሳክቶ እዚህ በመድረሱ የሃዘንሽ መጽናኛ ከሆነልኝ እንኳን ደስ አለሽ፤ በረከት ስምዖን 
የውሸት ጋጋታህ የክፋት ፕሮፓጋንዳህ ኢትዮጽያዊነት የማወረዱ አላማህ ግቡን መቷልና ከነሳውዲው 
ቱጃር ወዳጅህ እንኳን ደስ አለህ፤ ደብረጽዮን ገብረሚካዔልና ጌታቸው አሰፋ የገደላው መሃንዲሶች 
የአፈናው ሊቃውንቶች እንኳን ደስ አላችሁ ስታሳድዱት ያመለጣችሁን ሁን ብላችሁ ከፍታችሁ 
ባደላችሁት የባርነት ማረጋገጫ ፓስፖርት ሃገሩን እንዲለቅ ያደረጋችሁት ትኩስ ትውልድ ይህው ደሙ 
ደመከልብ ሆኖ ከውሻ አንሶ በዚህ ዘመን የሰውልጅ 
ሊቀበለው የማይችለውን ግፍ እየተቀበለ በመሆኑ 
የጥላቻ የበቀልና የዘር ማጥፋት ዘመቻችሁ ስኬት 
በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ። በአጠቃላይ መላው 
የትግሬው ነጻ አውጪ አባላትና ደጋፊዎች 
የዘበታችሁበት ኢትዮጽያዊነት የቀለዳችሁበት 
ኢትዮጽያዊ ዜጋ የመንግስታችሁ ደብል ድጂት 
የልማት በረከት ይህ የሃገርና የወገን ውርደት ስቃይ 
በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ። 
ኢትዮጽያና ኢትዮጽያዊነት ክብርና ኩራት ጀግንነትና 
አትንኩኝ ባይነት እንግዳ ተቀባይነት ደግነት የመሆኑ ታሪክ 
ተለውጦ አዋርደው ለውርደት ገለው ለገዳይ ሰድበው ለሰዳቢ 
አሳልፈው የሰጡን የሃገራችን አንጡራ ሃብት እየዘረፉ 
በቅንጦት ህይወት አለማቸውን ከመቅጨት በቢሊዮን ዶላር 
የሚቆጠር ገንዘብ ከሃገር አሽሸተው ሰርቶ የመኖር ነግዶ 
የመክበር አርሶና ቆፍሮ ኑሮን የማሸነፉን እድል ያሰጡት 
ትውልድ ህይወት ቢከብደው ተስፋው ቢጨልም ስደትን 
አማራጭ አድርጎ በላብ በወዙ ጥሮ ግሮ ህይወቱን ሊለውጥ ቤተሰቡን ሊረዳ የሄደበት የመከራ መንገድ  

እሱም በዝቶ ሬሳው በየመንገዱ ሲጎተት እየታየ ሴቶች በማንም ደደብ አራዊት ጀማላ በግፍ ሲደፈሩ ሃገር 
እመራለሁ የሚለው የትግሬ ወያኔዎች ጥርቃሞ ትንሽ ለማስመሰል ያህል እንኳ ግፉን ለማቆም ከመሞከር 
ይልቅ የሚባለው ተጋኗል ያን ያህል ችግር የለም የሚል መግለጫ ሲሰጡ አድምጠናል ጎበዝ ከአስር ሰው 
በላይ በተገደለበት በመቶዎች የአካል ጉዳተኛ በሆኑበት በአስር ሺዎች በግፍ ሃብትና ንብረታቸው 
እየተቀማ በየእስር ቤቱ ሲታጎሩ ጉዳቱን አቅሎ ማየት ፖለቲካ ነው ዲፕሎማሲ ወይስ ዘረኝነት የዛሬ 
ስምንት አመት ትግሬ ወደ መቀሌ እቃ ወደ ቀበሌ የሚል የባልቴቶች ተረት ይዞ ሁለት መቶ ሰዎች 
ለመግደል የበቃው ይህ ጠባብ ቡድን ጉዳዩን ማሰነሱ የጥላቻው ልኬታና ለኢትዮጽያውያን እንግልት 
ያለውን ፍላጎት ከማሳየት የዘለለ አለመሆኑን ዳግም ያረጋገጠበት አጋጣሚ ነው። 
በሃገራችን የትግሬ ነጻ አውጪ ወያኔዎች ገበሬውን 
ከእርሻው ነዋሪውን ከቅዬው በግፍ እያፈናቀሉ መድረሻ 
በማሳጣት በዶላር ሄክታር ለምና ድንግል መሬታችንን ለሳውዲ 
አራሾች እያከራየ መጤ አረቦችን ብረት ለበስ በታጠቀ ሰራዊት 
በማስጠበቅ ተቃውሞ ሊያቀርብ የሞከረውን በፊታቸው 
እየገደለ እያሰረ ያቃለለውን ኢትዮጽያዊ ወገን እንዲህ 
በሃገራቸው ቢያዋርዱት የሚደንቅ አይደለም። የሃገሩ መንግስት 
እንደሰው ሲያከብረው ያላዩትን (በጋንቤላ የተፈጸመውን ጅምላ 
ፍጅት በኦጋዴ የተደረሰው ዘር ማጥፋት በአፋር ወገኖች ላይ የተቃጣው ጥቃት በጉራፈርዳና በቤኒሻንጉል 
በአማራ ተወላጆቸ ላይ የተካሄደውን ያለ አንዳች ህጋዊ መሰረትና ማስጠንቀቂያ የተካሄደውን ሽብር ያዩት 
የሳውዲ ራቢጣዎች ይህንን በሃገራቸው ቢደግሙት ጥፋተኛው ማን ነው። በአጼውና በደርጉ ዘመን 
እንዲህ ያለ ብሄራዊ ውርደት በወገን ላይ ተቃጥቶ አያውቅም። 
 ‘’ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ’’ 
ይላል የሃገሬ ሰው ልጁ የሚያወርደው አባት 
ከማህበረሰቡ አክበሮት የሚሰጠው እንደሌለ ሁሉ 
የትውልድ ሃገሩ መንግስት ዜጋዬ ያላለውን ዘብ 
ያልቆመለትን የኔ ያላላለውን ከቶስ ሌላው እንዴት 
እንዲያከብረው እንጠብቃለን እንኳን ሳውዲ 
የነዳጅ ሃብት ዲታ ያደረጋቸውን ቀርቶ ዛሬ ወገኖቼ 
ኢትዮጽያዊ ሱዳንና ኬንያ እንኳ ሳይቀር 
እንደሰውያማይታይበት ደረጃ ደርሷል። ለዚህ ደግሞ ሃገራችንን የተቆጣጠረው የዘረኛ አገዛዙ እድሜ 
ከማራዘም ውጪ ቅንጣት ሃገራዊ ራዕይ የሌለው የትግሬ ወያኔዎች ቡድን ለጎረቤት ሃገራት የኬላና የፀጥታ 
ሃይሎች ጉቦ በመስጠት ኢትዮጽያዊው ዜጋ የለውጥ እንቅስቃሴ ያደርግብኛል ከሚል ፍርሃት ድንበር 
አልፎ በስደተኛው ላይ ሳይቀር ግድያ ፈጽሞ እየወጣ ሲገልና ሲያዋርደው እያዩ እንዴት ይራሩልን። ወያኔ 
ድንበር አልፎ በጎረቤት ሃገራት ውስጥ ይህን የመሰለ ግፍ መፈጸም ብቻ ሳይሆን በነዚሁ ድንበረተኞቻችን 
በኩል የለውጥ ትግል እንዳይካሄድ በሺህ ኪሎ ሜትር የሚቆጠር ለም መሬታችንን አሳልፎ እጅ መንሻ 
እስከመስጠት የደረሰ ሃገር ሻጭ ብሄራዊ ክህደት የሚፈጽም በፖለቲካ ግልሙትና የዘቀጠ አገዛዝ 
ኢትዮጽያ ውስጥ መኖሩን የሚያውቀው ዓለም ተሸክመን ያለንውን ወራዳ አገዛዝ ከላያችን ለማውረድ 
ያልቻልን ደካሞች መሆናችንን እያየ እንዴት ያክብረን የመዋረዳችን ምክንያቱ የዛች ሃገር ዜጋ ነን የምንል 
ሁላችንም ነን። የአባቶቻችን ልጆች መሆን ያቃተን ፈሪና ደካማ ስለሆን ነው።  

በአሁኑ ወቅት ስደትና መከራ በመጋራት በአለም ፊት ግንባር ቀደም የሆኑት የኢትዮጽያና የኤርትራ 
ህዝብ ሆኖ እያለ በጎረቤትም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ያሉ ኤርትራውያን ላይ እንዲህ ያላ ጥቃት 
እንዳይኖር የሃገራቸው መንግስት አቅሙ የፈቀደውን እንደሚያደርግ ይደመጣል።ዜጎቹም ላይ እንዲህ 
እንደኛ ያለ ግፍነና በደል ብዙም አይስተዋልም። ይህ የሚያሳየው ሻብያ ምንም ይሁን ምን ለዜጎቹ ደህንነት 
ዘብ የመቆሙን ሁኔታ የሚያሰረዳ ሁኔታ ነው። የትግሬ ነጻ አውጪ ወያኔዎች በመላው ዓለም ባሉት 
ኤንባሲዎች ውስጥ ያሉት ዲፕሎማት ተብዬዎቹ እንደሚባለው ሻንጣ ተሸካሚ ፤ በድርጅትና ፖለቲካና 
በግል ቢዝነሳቸው ላይ ስለሚያተኩሩ የዲፕሎማሲና የተመደቡበትን ሃገር ቋንቋና የፖለቲካ አካሄድ በቅጡ 
ያልተረዱት እውቀት አጠሮች ስለሆኑ ብቻ አይደለም ለኢትዮጽያውያን ሰቆቃ ምላሽ የማይሰጡት ዋናው 
ቁልፉ ችግራቸው ከራሳቸው ጎጥ ውጪ ያለውን እንደ ተቃወሚና እንደ ጠላት የሚቆጥሩ ዘረኞች ስለሆኑ 
ነው። እዚህ ላይ አንድ የመን የነበረ ወገን ሲያጫውተኝ ለይስሙላ ከላይ ለይምሰል ከሚቀመጡት የሌሎች 
ብሄር አባላት ስር በየኤንባሲው የሚቀመጡት የትግራይ ተወላጆች ከራሳቸው አካባቢ ሰው በስተቀር 
ሌላውን ኢትዮጽያዊ በክፉ የሚመለከቱ በመሆናቸው እንኳን ሊረዱን ይቅርና ለየመን የደህንነት መስሪያ 
ቤት አሳልፈው እስከመስጠት በደል ሲፈጽሙብን ነበር ሲል በሃዘን የነገረኝ ነው ከላይ በጥቅስ ውስጥ 
ያለውን ከዛው ከሳውዲ ሰቆቃ ውስጥ ያለች እህታችን ለኢሳት የገለጸችው። 
 እንኳን የነጻነት ጭለማ በዋጠው የአረብ ሃገራት 
ይቅርና በሰሜን አሜሪካ ያለው ኤንባሲ ከነስሙም (የወያኔ 
ኤንባሲ) በሚል መታወቅ የደረሰ የትግራይ ልማት ማህበር፤ 
የትግራይ ሴቶች፥ ወጣቶች፤ወዘተ በሚል የአንድ አካባቢ 
ሰዎች የሚሰበሰቡበት ዳንኪራ የሚረግጡበት የኢትዮጽያ 
ህዝብን ለመከፋፈልና አንገት ለማስደፋት የሚወጠንበት 
ከግማሽ ሚሊዮን የማያንስ ኢትዮጽያዊ ባለበት አካባቢ 
የአንድ ጎጥ ሰዎች ቁጥጥር ስር የመዋሉ እውነታ ለሚያውቅ 
ሃብታችንን እንዲፈነጩበት መሬታችንን በልግስና 
በሠጣቸው የመካከለኛው ምስራቅ ሃገሮች ያለው የወያኔ ዲፕሎማሲ የመዋቅር መዘውር በጎጠኝነት 
የተተበተበ በጥቅምና በጥላቻ የተጠነጠነ በመሆኑ በሃገር ውስጥ በትውልድ ማንነቱ በኦሮሞነቱ፤
በአማራነቱ፤በአፋርና ፤ጋንቤላነቱ እየለዩ እንደሚያስሩት እንደሚገሉትና እንደሚያሰቃዩት ሁሉ በስደትም 
ስቃዩ የሚበዛው እንግልቱ የነገሰው በሃገሩ የመኖር ነጻነት የገፈፉት ህብረተሰብ እሱው በመሆኑ በሌሎች 
ቢንገላታ ቢዋረድ ቢሞት ሬሳው ቢጎተት ግዳቸውም ምንድን ነው እነሱው የሚያደርጉት አይደለም እንዴ 
ስለዚህ ቀደሚና ዋና ጠላታችን የትግራይ ነጻ አውጪ ወያኔ ለመሆኑ ከዚህ በላይ ምን ማስረጃ ማቅረብ 
ያስፈልጋል። 
ባለፉት 22 አመታት ብዙ ተወርቷል አያሌ መስዋዕትነት ተከፍሏል ውጤቱ መታሰር መጋዝ 
መሞት መዋረድን አልገታም እስከ መቼ ታሪክ አውሪ ከመሆን አልፈን ታሪከ ሠሪ የምንሆነው መቼ ነው። 
እስከመቼስ ነው በላያችን የተንሰራፋውን ሌባ ዘራፊና ዘረኛ ወያኔን የምንሸከመው ፤ ስደቱ መፍትሄ 
አልሆነም ዝምታው አልሰራም ሞት እስራትና እንግልት አልተለየንም፤ ስደታችን ውርደት በሃገር መኖራችን 
ረሃብ ቸነፈር ተስፋ መቁረጥ ይህ ሁሉእስከመቼ ማብቂያው የት ላይ ነው እርሻችንን እየነጠቀ ለውጭ 
ባለሃብት የሚሸጥ ፤ንብረታችንን እየቀማ ክልልህ አይደለም ውጣ ተብለን ያፈራንውን ሃብት ተቀምተን 
ለጎዳና ፤ገዳማችንን እያፈረሰ ሸንበቆ የሚተክል መስኪዳችንን የካድሬ መናሃሪያ ያደረገ ከዚህ ሁሉ አልፎ 
ጸጥታ አስከባሪ የተባሉት የወያኔ አፋኞች በዜጎች ላይ ግብረሰዶም ወደመፈጸም ክብራችንን ያወረደውና 
አሳልፎ ለአዋራጅ የሰጠህ ወገኔ ሆይ የትግሬ ነጻ አውጪ ወያኔ ነው።የእነሱ ልጆች ከኛ በተቀማ ሃብት  

አውሮፓና አሜሪካ በውድ ኮሌጆች ይማራሉ፤ ከኛ በተቀማ ገንዘብ የገላቸውን ጭቅቅት የጎፈሬያቸውን 
ተባይ የእግራቸውን ንቃቃት አራግፈው እኛ ጥሬ መቆርጠም ዳገት ሆኖብን እነሱ ቁርሳቸው ሻኛ 
ትራሳቸው ጮማ ሆኖ በላያችን ላይ የሚዘባነኑት ከደደቢት የወርቅ ጭብጦ ይዘው መጥተው አይደለም ። 
ወገናችን ሆዱን ምግብ እያማራው ገላው በእጦት ተራቁቶ የጣር ህይወት እንዲገፋ የፈረደበት ይህ የወያኔ 
ድኩማን ቡድን ነው። እንዲህ በላያችን የነገሰው ከሰማይ ተቀብቶ ወይም የተለየ ችሎታ ኖሮት ሳይሆን 
በእኛ ፍርሃት አለመተባበር ደካማነት ብቻ ነው። ስለሆነም የፍርሃት ቀንበርን የግለኝነት አባዜን ወደጎን 
ጥለን በቀዳሚውና በዋናው ጠላታችን የወያኔ ቡድን ላይ እናንሳ ያኔ የመጨረሻው መጀመሪያ ይሆናል። 
የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የድህረገጽ ዝግጅት ክፍሎች በአርቲ ቡርቲ አጀንዳ የተጠመዳችሁ 
የመንደር ሬድዮ ጣቢያዎች ርዕስ አጥታችሁ የስድብ ወጀብ ለምታዘንቡ የፓልቶክ ክፍሎች የወገን ውርደት 
ይበቃ ዘንድ የትውልዱ መከራ መፍትሔ እንዳያገኝ ጠፍሮ የያዘንን አሮጌና ኋላ ቀር ኢዲሞክራሲያዊ 
የፖለቲካ ባህል ወደ ጎን በማድረግ በአንድነትና በጋራ ለተደራራቢና ተደጋጋሚ ችግር እየዳረገን ያለውን 
ሰውበላ ትውልድ አምካኙን የወያኔን አገዛዝ በማስወገድ ላይ ሃይላችሁንና እውቀታችሁን በማስተባበር 
ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ስር ነቀል ሕዝባዊ ንቅናቄ የሚካሄድበት ሁኔታ ለማመቻቸት በጋራ እንድትቆሙ 
ተገቢውን የቅስቀሳና የማንቃት ሚና ለመጫወት እንድትነሱ የወገን መከራ የሃገር ህልውና ግድ ይላችኋል። 
ኢትዮጽያዊ ነኝ የምትል ኳስ ጨዋታ አለ ስትባል ባንዲራ ለብሰህ እምቢልታ የምትነፋው ቦታ አልበቃ 
የሚልህ የሃገርህን ቡድን ለመደገፍ በነቂስ የምትወጣው ወጣት ይህን ማድረግህ መልካም ነው ተገቢም 
የሚደገፍም ነው። የወንድሞችህ አናት በጥይት ሲነደል ወገባቸው በቆመጥ ሲጎብጥ ለቅሪላው ግዜ 
የምታነግባትን ባንዲራ ለብሰህ ወገንህን ላይ ግፍ የፈጸሙትን የአረመኔው የሳውዲ መንግስት ኤንባሲዎችና 
በወገን መከራ በሚነግደው የወያኔ አገዛዝ ላይ በያለህበት በነቂስ በመውጣት ተቃውሞህን በማሰማት 
ወገናዊ ድርሻህን ተወጣ። 
አዲሱ ትውልድ ወጣቱ ሆይ ስደት ይብቃህ ለለውጥ ተነስ ወይ በተገቢው ለመኖር አለያም 
ለክብር ሞት ራስህን አዘጋጅ የአህዛብ መቀለጃ የደደቦች መጫዎቻ የመሆን ታሪክህን አድስ፤ ሃገርህ እንኳን 
ላንተ ለነዚህ ደንቆሮ ጀማላዎች የተረፈ ወርቅ ተፈጥሮ አላት፤ ከበረታህ አንተ ሳትሆን እነሱ ወዳንተ 
ይመጣሉ። ትላንትም በአባቶችህ ዘመን ክፉ ቀን በክብር ያሳለፉት ባንተ ሃገር ነበር፤ እንዲህ ሊያወርዱህ 
እድል ያገኙት ሃገርህን የወረረው የትግሬ ነፃ አውጪ ሌባ ቀማኛና ሰዶማዊ አገዛዝ ታፍሮና ተከብሮ የኖረ 
ሃገራዊና ታሪካዊ ክብርህን በዓለም ፊት ያቀለለ በመሆኑ ክንድህን ማንሳት ያለብህ በዚህ ሃገር በቀል 
የአረቦች የጭን ገረድ በሆነ የወያኔ አገዛዝ ላይ ነው ። ስለዚህም በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ 
በሰላም ይሁን በአመጽ በጓንዴ ይሁን በጎራዴ በቀለም ይሁን በፍራፍሬ አብዮት ስደት በቃኝ ብለህ 
አገርህን ሳትለቅ ለውርደትና ለስቃይ አሳልፎ የሠጠህን መሪር ጠላትህ የሆነውን የወያኔ ቡድን አፈርድሜ 
ለማስጋጥ ተነስ፤ ታጠቅ፤ ዝመት፤ የውርደት ማርከሻ መድሃኒቱ እንደአባቶችህ እንቢኝ በማለት ባንዳና 
ቅጥረኛውን ማስወገድ ብቻ ነው። ይቻላል! ተችሏልም!! የግድ መቻልም አለበት!! 
 ከዘላለም ባርነት የአንድ ቀን ነጻነት!!! 



Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar