tirsdag 24. mai 2016

ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ!

ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ!

ህወሃት 25 አመታት ሙሉ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ገንብቻለው እያለ መደስኮሩን ተያይዞታል። የህወሓት ገንብቻለው የሚለው ዲሞክራሲው ከወረቀትና ከአፍ ባልዘለለ መልኩ ሲነገርለት የሚኖረው ይህ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት አንድም ቀን በህዝቦች መካከል በስራ ላይ ሳይወል ይህው በወሬ ብቻ ሆኖ ቀረ።

ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር እንደታገሉ የሚነግሩን ህወሓቶች አንዲትም ቀን ለህዝቡ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት በተሞላበት መልኩ ለህዝቡም ሆን ለሀገሪቱ ሲሰሩ አይስተዋሉም። ከላይ እንደገለፅኩት የህወሓት ዲሞክራሲ ከወረቀትና ከአፍ ባልዘለለ መልኩ በምንም ላይ ሲተገበር አይታይም።

ዲሞክራሲ ማለት የመናገር መብት፣ የመፃፍ መበት፣  የመደራጀት መብት፣ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት እነዚህ ሁኔታ በሌሉበት እንዴት ነው ዲሞክራሲን በሀገሪቱ ላይ አምጥተናል ብለው መነገሩ። እውን ህወሓት ዲሞክራሲን እንዴት አድርጎ ቢተረጉመው ነው የታገልነው ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ነው ሲል። እርግጥ ነው በህወሓት ለህዝቡ የመታሰር፣ የመገደል፣ የመታፈን፣ የመሰደድ፣ የመፈናቀል፣ የመታፈን ስርዓት ገንብቷል ይህ የማይካድ ሀቀ ነው።

ዲሞክራሲ በሌለበት ሀገር ውስጥ ለህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተገንብቷል ብሎ ማሰቡ እጅግ ሞኝነት ነው። ዜጎች የመኖር ህልውናቸው አጣብቂኝ ውስጥ ባለበት ሀገር ውስጥ ዲሞክራሲ አለ ብሎ መናገሩ እራስን እያታለሉ መኖር ማለት ነው። ለህዝቡ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንደታገሉ ቢናገሩም ነገር ግን እነሱ የታገሉለት ዋነኛ አላማ የህዝቦችንና የሀገር ታሪክ ማጥፋትና የህዝቡን ሀብት ለመዝበር ነው። ህወሓት ስልጣኑን የያዘው በዲሞክራሲያዊ ስርዓት በህዝብ ተመርጦ የህዝብን ይሁንታ አግኝቶ የመጣ ስርዓት አይደለም፤ በሃይል ስልጣን ያዘ፤ በሃይል ሀገርና ህዝብን የገዛ ያለ ስርዓት ነው።


በእነዚህ ሁለት አስርት አመታት ውስጥ ህወሓት ክ፫ ያላነሱ ምርጫዎችን ቢያደርግም አንዱንም ጊዜ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አላደረገም። ይህ ባለበት ሁኔታ ላይ እለት ተዕለት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንደገነቡ ቢነግሩንም ሀቁ ግን በሀገሪቱና በህዝቦቹ ላይ የሚፈፀመው ኢፍት ሃዊ ድርጊቶች ሲፈፀሙና እየተፈፀሙ ያሉ ናቸው። ከ1997  ምርጫ ወዲህ በሀገሪቱ ላይ ምንም አይነት የዲሞክራሲ ባልታየበት ገነባነው ያሉትም ዲሞክራሲ ለዜጎች ፍትህ ሲያጓድል እንጂ ፍትህ ሲሰጥ አልተመለከትንም። የ1997 ዓም ምርጫ ተከትሎ ህወሓት ለስልጣኑ በመስጋት የተለያዩ አዋጆችን በማፅደቅ የመፃፍም ሆን የመናገር እንዲሁም የመደራጀት መብት እንዳይኖራቸው በማድረግ ህግ አውጥቶ አፅድቋል።

ይህን ተከትሎ ለዚሁ ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር ቀላል የሚባሉ አይደለም። በተለይ ፀረ ሽብር ህጉ አዋጅ ሆኖ ከፀደቀ ወዲህ ብዙን ምክንያትና አጋጣሚን እየጠበቁ ህዝቡን ለእስር እየተዳረጉ ይገኛል። ለዚህም ይህ አዋጅ ለሚፅፉ፣ ለሚደራጁ እንዲሁም ሀሳብን በነፃ ለሚገልፁ ለማፈን የወጣ ህግ ነው። ይህ ባለበት ሁኔታም ከህወሓት ጋር እየተናነቁ ያሉም ሀገርና ህዝብ ወዳድ ኢትዮጵያዊያን እጅግ የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው። ይህና መሰል ችግሮች ባለበት ሀገራችን ላይ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተገንብቷል ብሎ ከማለት "ሳይገነባ የፈረሰ ዲሞክራሲ" ቢባል ጥሩ ነው። ባይ ነኝ እኔ

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ

tirsdag 17. mai 2016

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ!
የዘንድሮን የግንቦት 20 በአል ስታከብሩ እነዚህ ስቃይና በደሎች ያሰባቹ መሆን አለበት። ግንቦት 20 የህዝብ በአል ነው ብሎ ማሰብ በህዝቡ ደምና በሞቱት ህይወት መቀለድ ነው።ህወሓት የስልጣን ዘመኑ ለማራዘም የገደለውን ገድሎ፣ያሰረውን አስሮ፣ያፈነውን አፍኖ ስልጣኑን በሃይል በመጠቀም ላይ ነው። ገና ከጅምሩ በጫካ በነበሩ ጊዜ ሲያቅዱ የነበረውን ነው አሁን እየፈፀሙ የሚገኙት ይህ ደግሞ እውነታ ከቀድሞ የህወሓት ሃላፊ የነበሩ አቶ ገ/መድህን አርያ የተናገሩት ሀቅ ነው።
Ginbot 20 Ferewoche
ይህን በአል ልታከብሩት የምትችሉት ህወሓቶችና ቤተሰቦቻችሁን እንዲሁም የትግራይ ካድሬዎች ብቻና ብቻ ነው። ይህን ያልኩበት ምክንያት ግልፅና ግልፅ ነው። በዚህ ስርዓት ውስጥ አብዛኛው ለትግራይ ተወላጆች ጥሩ እድል ፈጥሯል። ይህ የማይካድ ሀቅ ነው። ታዲያ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን የአንድ ብሄር ቢባል ምኑ ነው ውሽት!

የኢትዮጵያን ህዝብ በግንቦት 20 ያገኛው ድል ሳይሆን ውርደት ነው፤ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታ ነው። ስለግንቦት 20 ከድል ይልቅ ወርደቱ ጎልቶ የታየበት ወቅት ነው። እውነት በዚህ ወቅት በህወሓት በህዝቡ ላይ የሚፈፅመው ግፍና መከራ ተዘንግቶን ነው? በቅርቡ እንኳን በኦሮሚያ፣በአማራ በደቡብ ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ፣በኮንሶ፣በጋምቤላ ወገኖቻን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እንዲሁም ቀን በቀን የሚታሰረው ወገኖች እነዚህ ታዲያ የግንቦት 20 ፍሬዎች ቢባሉ ምን ይወጣላቸዋል።


ይሄን እውነታ ሁላችንም ጠንቅቀን እንረዳለን ዳሩ ግን ዝምታችን ወደር አቶ ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ክፉኛ ተለማመድ ነው መሰል ስምተንም ሆነ አይተን እኛ ግን እዛው የተቀመጥንበት ላይ ነን!!!!! ታዲያ የእኛ ተቃውሞ ምኑ ጋር ነው? መቃወም ብቻ ለውጥ አያመጣም፤እየተቃወምን ያለው ተደራጅተን ነው ወይስ እንዲሁ ነው? ሳንደራጅ፣ሳንሰባሰብ መቃወሙ ትርጉም አይኖረውም።
ስለዚህ እንሰባሰብ፣እንደራጅ፣እንመከከር . . . . . . . ከዛን ተቃውሟችን ለአንድ ህዝብ እስከሆነ ድረስ አሁን እየደረሰብን ያለውን ግፍና መከራ ከወሬ በዘለለ መልኩ ወደተግባር እንለውጠው።

ህወሓቶች ህዝብና ሀገር ለማጥፋት አንድ ሆነዋል። እኛ ሀገርና ህዝብን ለማዳን እንዴት እንድ መሆን አቃተን? ለነገሩ ለጥሩ ነገር ህብረት ሃይል የለውም፤ለመጥፎ ነገር ግን ህብረት ሃይል አለው። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወቅቱ የሚፈልገው ህብረትና አንድነት ነው። ይህን ህብረትና አንድነት ህወሓቶች ደግሞ አይፈልጉትም። ይህ ስርዓት በዚህ አይነት ከቀጠለ የህዝባችን ስቃይና መከራ እንደሚቀጥል እሙን ነው።

የግንቦት 20 ፍሬዎች መግደል፣መታሰር፣መታፈን፣መፈናቀል እንዲሁም መሰደድ ሲሆኑ በ25 አመታት ውስጥ እነዚሁ በህወሓት ሲተገበሩና እየተተገበሩ ያሉ ናቸው።


 የሁላችንም ችግር ህወሓትና ስርዓቱ ነው!



ፎቶዎችን በመሰብሰብና በማስተካከል የፌስቡክ ጓደኞቼ የረዱኝ ናትናኤል መኮንን እና ጥላዬ ታረቀኝ ከልብ አመሰግናለሁ።


የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የግንቦት 20 ፍሬዎች ከብዙ በጥቂቱ!

የዘንድሮን የግንቦት 20 በአል ስታከብሩ እነዚህ ስቃይና በደሎች ያሰባቹ መሆን አለበት። ግንቦት 20 የህዝብ በአል ነው ብሎ ማሰብ በህዝቡ ደምና በሞቱት ህይወት መቀለድ ነው።ህወሓት የስልጣን ዘመኑ ለማራዘም የገደለውን ገድሎ፣ያሰረውን አስሮ፣ያፈነውን አፍኖ ስልጣኑን በሃይል በመጠቀም ላይ ነው። ገና ከጅምሩ በጫካ በነበሩ ጊዜ ሲያቅዱ የነበረውን ነው አሁን እየፈፀሙ የሚገኙት ይህ ደግሞ እውነታ ከቀድሞ የህወሓት ሃላፊ የነበሩ አቶ ገ/መድህን አርያ የተናገሩት ሀቅ ነው።

ይህን በአል ልታከብሩት የምትችሉት ህወሓቶችና ቤተሰቦቻችሁን እንዲሁም የትግራይ ካድሬዎች ብቻና ብቻ ነው። ይህን ያልኩበት ምክንያት ግልፅና ግልፅ ነው። በዚህ ስርዓት ውስጥ አብዛኛው ለትግራይ ተወላጆች ጥሩ እድል ፈጥሯል። ይህ የማይካድ ሀቅ ነው። ታዲያ ግንቦት 20 ለኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን የአንድ ብሄር ቢባል ምኑ ነው ውሽት!
የኢትዮጵያን ህዝብ በግንቦት 20 ያገኛው ድል ሳይሆን ውርደት ነው፤ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታ ነው። ስለግንቦት 20 ከድል ይልቅ ወርደቱ ጎልቶ የታየበት ወቅት ነው። እውነት በዚህ ወቅት በህወሓት በህዝቡ ላይ የሚፈፅመው ግፍና መከራ ተዘንግቶን ነው? በቅርቡ እንኳን በኦሮሚያ፣በአማራ በደቡብ ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ፣በኮንሶ፣በጋምቤላ ወገኖቻን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እንዲሁም ቀን በቀን የሚታሰረው ወገኖች እነዚህ ታዲያ የግንቦት 20 ፍሬዎች ቢባሉ ምን ይወጣላቸዋል።

ይሄን እውነታ ሁላችንም ጠንቅቀን እንረዳለን ዳሩ ግን ዝምታችን ወደር አቶ ይህን ሁሉ ግፍና መከራ ክፉኛ ተለማመድ ነው መሰል ስምተንም ሆነ አይተን እኛ ግን እዛው የተቀመጥንበት ላይ ነን!!!!! ታዲያ የእኛ ተቃውሞ ምኑ ጋር ነው? መቃወም ብቻ ለውጥ አያመጣም፤እየተቃወምን ያለው ተደራጅተን ነው ወይስ እንዲሁ ነው? ሳንደራጅ፣ሳንሰባሰብ መቃወሙ ትርጉም አይኖረውም።
ስለዚህ እንሰባሰብ፣እንደራጅ፣እንመከከር . . . . . . . ከዛን ተቃውሟችን ለአንድ ህዝብ እስከሆነ ድረስ አሁን እየደረሰብን ያለውን ግፍና መከራ ከወሬ በዘለለ መልኩ ወደተግባር እንለውጠው።

ህወሓቶች ህዝብና ሀገር ለማጥፋት አንድ ሆነዋል። እኛ ሀገርና ህዝብን ለማዳን እንዴት እንድ መሆን አቃተን? ለነገሩ ለጥሩ ነገር ህብረት ሃይል የለውም፤ለመጥፎ ነገር ግን ህብረት ሃይል አለው። አሁንም ጊዜው አልረፈደም ወቅቱ የሚፈልገው ህብረትና አንድነት ነው። ይህን ህብረትና አንድነት ህወሓቶች ደግሞ አይፈልጉትም። ይህ ስርዓት በዚህ አይነት ከቀጠለ የህዝባችን ስቃይና መከራ እንደሚቀጥል እሙን ነው።

የግንቦት 20 ፍሬዎች መግደል፣መታሰር፣መታፈን፣መፈናቀል እንዲሁም መሰደድ ሲሆኑ በ25  አመታት ውስጥ እነዚሁ በህወሓት ሲተገበሩና እየተተገበሩ ያሉ ናቸው።

ፎቶዎችን በመሰብሰብና በማስተካከል የፌስቡክ ጓደኞቼ የረዱኝ ናትናኤል መኮንን እና ጥላዬ ታረቀኝ ከልብ አመሰግናለሁ።

ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ!

የሁላችንም ችግር ህወሓትና ስርዓቱ ነው!