onsdag 11. desember 2013

የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ የመንግሥት ተቋማት የኢንተርኔት መረጃዎችን ሚስጥራዊ ሊያደርግ ነው

ተቋማቱ በኤጀንሲው የተሠራውን ‹‹ዳጉ ሜይል›› መጠቀም ይገደዳሉ

የመረጃ ደኅንነት ኤጀንሲ በቅርቡ በፀደቀው አዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ቁልፍ የመንግሥት ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችና ኢንተርኔትን መሠረት ያደረጉ የመረጃ ልውውጦች ከኢንተርኔት ‹‹ሃከሮች›› (በርባሪዎች) ለመከላከል የሚያስችል ቴክኖሎጂ ይፋ ሊያደርግ ነው፡፡
ቁልፍ የሚባሉ የመንግሥት ተቋማት እንደ ጂ-ሜይል (Gmail) ያሉ የኢንተርኔት መልዕክት ማስተላለፊያዎችን እንዳይጠቀሙ ሊገደዱ ነው፡፡
insa-ethiopia1-620x310
ኤጀንሲው በቅርቡ ተግባራዊ ለማድረግ እያበለፀገ የሚገኘው ቴክኖሎጂ ቁልፍ የሚባሉ የመንግሥት ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመረጃ ልውውጥንና የመረጃ ማኅደርን ሚስጥራዊ የሚያደርግ መሆኑን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
በእንግሊዝኛ ስያሜው ‹‹ፐብሊክ ኪይ ኢንፍራስትራክቸር›› በሚል የሚታወቀውና በርካታ የዓለም አገሮችና ግዙፍ የሚባሉ ተቋማት በአሁኑ ወቅት የሚጠቀሙበት ውድ የቴክኖሎጂ ውጤት ሲሆን፣ ኤጀንሲው ይህንን ቴክኖሎጂ በራሱ የሰው ኃይል እንዳበለፀገው ለመረዳት ተችሏል፡፡
የቴክኖሎጂ ውጤቱ በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ ሲገመት፣ ተግባራዊ በሚሆንበት ወቅትም ቁልፍ የሆኑ የመንግሥት ተቋማት የመረጃ ልውውጣቸውን በዚህ ቴክኖሎጂ ለማድረግ ይገደዳሉ፡፡
ቴክኖሎጂው በኢንፎርሜሽን ደኅንነት መስክ ‹‹ክሪፕቶግራፊ›› በሚል የሚታወቀውን የመረጃ ደኅንነት አገልግሎት በተቋማቱ ሥራ ላይ እንዲውል ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ ‹‹ክሪፕቶግራፊ›› ማለት በኢንተርኔት ወይም በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የሚተላለፍ ወይም የተቀመጡ መረጃዎችን መረጃው ከሚላክለት ተቀባይ በስተቀር ማንኛውም አካል ወይም የቴክኖሎጂ ውጤት መረጃውን እንዳያነበው ወይም እንዳይቀይረው የሚያስችል የመረጃ ምስጠራ ሳይንስ ነው፡፡
ኤጀንሲውን በድጋሚ እንዲቋቋም ያደረገው በቅርቡ የፀደቀው አዋጅ ለኤጀንሲው ከሰጣቸው ኃላፊነቶች መካከል ይህ የ‹‹ክሪፕቶግራፊ›› ወይም የመረጃ ምስጠራ ተግባር አንዱ ነው፡፡
ይህ ኃላፊነት ለኤጀንሲው የተሰጠበትን ምክንያት ለማብራራት በደጋፊ ማስረጃነት ከአዋጁ ጋር የተያያዘው ማብራሪያ የተሻለ ደኅንነት አላቸው የሚባሉ አገሮች በራሳቸው ቴክኖሎጂ ላይ ብቻ ጥገኛ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ኢትዮጵያ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝና የቴክኖሎጂውን እውቀት ያካበቱ ዜጎችም በጣም ውስን መሆናቸውን ያብራራል፡፡
በዚህ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ በእጅጉ ኋላ የቀረች መሆኗንና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በስፋት አገልግሎት ላይ የዋሉ የኢንተርኔት መረጃ መለዋወጫ መንገዶች (ቴክኖሎጂዎች) አሜሪካ በሚገኙ ኩባንያዎች መበልፀጋቸውን ይገልጻል፡፡ እነዚህም የጐግል፣ የያሁና የቢንግ ሰርች ኢንጂኖች እንዲሁም የፌስቡክ ማኅበራዊ ድረ ገጽ በአጠቃላይ የሁሉም ሰርቨሮች የሚገኘው በአሜሪካ መሆኑን ያትታል፡፡
ከላይ በተጠቀሱ የኢንተርኔት ቴክኖሎጂ ሰርቨሮች በአሜሪካ የሚገኙ ናቸው ማለት አሜሪካ በሰርቨሮቹ የሚገኙ መረጃዎችን እንደልቧ ማግኘት የምትችል መሆኑን የአዋጁ አባሪ ማብራሪያ ያስረዳል፡፡ ሌላው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን ለአደጋ ተጋላጭ የሚያደርገው የቴክኖሎጂው መገልገያ መሣሪያዎች (እንደ ኮምፒውተርና ተዛማጅ መሣሪያዎች) በአምራቾች በሚፈበረኩበት ወቅት የተጋላጭነት ቀዳዳ (Back Doors) እንዲኖራቸው የሚደረግ እንደሆነና ይህም አምራቾች በፈለጉበት ወቅት በፈጠሩት ቀዳዳ ሠርገው በመግባት መረጃዎችን ከባለቤቱ ዕውቅና ውጭ እንደፈለጉ ማድረግ የሚያስችላቸው ነው፡፡
ኤጀንሲው በማገባደድ ላይ የሚገኘው የ‹‹ክሪፕቶግራፊ›› ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገው አገር አቀፍ የ‹‹ፐብሊክ ኢንፍራክትራክቸር›› ቢያንስ ቢያንስ ቁልፍ የሆኑ የመንግሥት ተቋማት መረጃዎችን ሚስጥራዊነት ወይም የመረጃው ባለቤትና ተቀባይ ባልሆኑ አካላት መነበብ ወይም መለወጥ እንዳይቻል ማድረግን በመሠረታዊነት ያካተተ ነው፡፡
በዚህ መሠረተ ልማት ከሚካተቱ የመንግሥት ተቋማት መካከል ፍርድ ቤቶች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ ኮምፒዩተራይዝድ የሆኑ ሥርዓቶችን የሚከተሉ ቁልፍ የመንግሥት ተቋማት መሆናቸውን ባለፈው ሳምንት ካካሄደው ዓውደ ርዕይ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ኤጀንሲው በራሱ የሰው ኃይል ያበለፀገው ‹‹ዳጉ ኢሜይል›› የሚል መጠሪያ የተሰጠው እንደ ‹‹ያሁ›› እና ‹‹ጂሜይል›› የኢንተርኔት መልዕክት መለዋወጫ ቴክኖሎጂ ማበልፀጉን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ‹‹ዳጉ ኢሜይል›› ከአፋር ብሔረሰብ የመረጃ መለዋወጫ ‹‹ዳጉ›› የተባለ ባህላዊ ሥርዓት መጠሪያ ስያሜውን እንዳገኘ በዓውደ ርዕዩ የተገለጸ ሲሆን፣ የሙከራ ትግበራው ተጠናቆ በኤጀንሲው ግቢ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
በቅርብ ጊዜ ውስጥ ‹‹ዳጉ ኢሜይል›› ወደ ተግባር የሚገባ መሆኑንና ቁልፍ የመንግሥት ተቋማት በዚህ ቴክኖሎጂ ብቻ የመጠቀም ግዴታ እንደሚጣልባቸው ለመረዳት ተችሏል፡፡
በቅርቡ ተግባራዊ ይደረጋሉ ተብለው የሚጠበቁት እነዚህ ቴክኖሎጂዎች ኤጀንሲው ሰሞኑን አካሂዶ በነበረው ዓውደ ርዕይ ላይ ይፋ ሆነዋል፡፡ ኤጀንሲው የቴሌኮም ማጭበርበርን የመከላከል ኃላፊነት በአዋጅ ካገኛቸው ሥልጣኖች አንዱ ሲሆን፣ በዚህ የደኅነነት አገልግሎት ላይ በስፋት መሥራት በጀመረ በጥቂት ዓመታት ጊዜ ውስጥ 1.75 ቢሊዮን ብር ኪሳራ መታደጉን አስረድቷል፡፡
ከኢትዮ ቴሌኮም ኔትወርክ ውጭ የስልክ ግንኙነት ከሌላው ዓለም ጋር በመፍጠር የተሰማሩ ወንጀለኞች መኖራቸውን የሚያስረዳው ኤጀንሲው የወንጀለኞቹ መረብ ከሕገወጥ ንግድ፣ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርና ከሽብር ጋር የተገናኘ መሆኑን አሳውቋል፡፡ በመሆኑም በዚህ የቴሌኮም ማጭበርበር አገሪቱ 2.7 ቢሊዮን ብር ማጣቷን፣ ኤጀንሲው በስፋት ከተንቀሳቀሰ በኋላ ግን 1.75 ቢሊዮን ብር ማዳን መቻሉንና 125 ሰዎችም በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጿል፡፡
በመረጃ ደኅንነት ዘርፍ በኢትዮጵያ ውስን እውቀት መኖሩ በገሃድ ያለ እውነት በመሆኑ፣ ይህንን ችግር ለመቅረፍም የመረጃ ደኅንነት ትምህርት በትምህርት ቤቶችና በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠት እንዳለበትና በዚህ ዙሪያም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት ላይ እንደሚገኝ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ reporter

 

søndag 8. desember 2013

ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት


ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን ነው፡፡ይህንንም ተከትሎ በመንግስት አሳሳቢነት እልፍ ሲልም አስገዳጅነት ህዳር 29 በየዓመቱ ከተለያዩ ጎሳ የተወጣጡ ሰዎች ተሰባስበው በመንግሰት ሹማምንቶች ፊት በአደባባይ ከበሮ የሚደለቅበት ቀን ነው፡፡ይሁን እንጂ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን መልካም ፍቃድና ተሳትፎ ባልታየበት የፀደቀው ህገ መንግስት በብዙሃን ዘንድ ተቀባይነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ነው፡፡በዚህም መሠረት ከቃሉ አጠቃቀም ጀምሮ እስከ አከባበሩ ክብረ በዓል አብዛኛዉ ሰው እኔንም ጨምሮ ግድ አይሰጠንም፡፡

‹‹ይህ ህገ-መንግስቱን የመነዳ ተግባር ነው!!!›› ከገዢው መንግስት ተደጋግሞ የሚሰማ ለመፈረጅ ወይም ለመከሰስ የሚጠቀሙበት ቃል ነው፡፡ አንድ ወዳጄ እንዲህ አለኝ ‹‹ ይህ ህገ መንግሰት ዝም ብሎ የተደረደረ ብሎኬት ነው እንዴ የሚናደው ?›› በማለት ሲተች ሰምቸዋለው፡፡በመናድ እና ደግፎ በማቆየት ላይ የተመሠረተሁን  ህገ መንግስት እጅግ በጣም ብዙ ነገር ተብሎለታል፡፡
እየተንገዳገደ ያለው ህገ መንግስት ከአፀዳደቁ ጀምሮ የሚቀሩት ድንጋጌዎች መኖራቸው ለማንም ግልፅነው፡፡ ቢሆንም ፀድቆ በተግባር ላይ የሚገኘው ህገ መንግስት ዋጋ እንዳይኖረው እያደረገ ያለው የገዢው መንግስት አካሄድና ተግባር መሆኑ በአጭሩ ለማሳየት እሞክራለው፡፡
1ኛ. መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ሃይማኖትም በመንግስት ጣልቃ አይገባም የሚለው በሕገ መንግስት አንቀጽ 11 ንዕሱ አንቀፅ 3 ተደንግጎ የሚገኝ ነው፡፡ይሁን እንጂ ገዢው መንግስት በሃይማኖት ላይ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት እየፈፀመ ይገኛል፤ለዚህም ጥሩ ማሳያ የሚሆነው በእስልምና አይማኖታ እየተፈፀመ ያለው በደል ነው፡፡በደሉ በይፋ የወጣ ሲሆን በተለይ ለእምነታችን እንቢኝ ያሉ ለሞት፣ለእስርና ለእንግልት ተዳርገው ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪ በኦርቶዶክስ እምነት ውስጥም ጣልቃ ገብነቱ እንደተጠበቀ ነው፡፡ገዳማትና አድባራት በልማት ስም ፈርሰዋል የተቀሩት ቦታቸው ተጎምዶ ተወስዶል በዚህም ምክንያት የሀይማኖት አባቶችና ጥቂት የማይባሉ የእምነቱ ተከታዮች ለእስርና ለእንግልት ተዳርገዋል፡፡
ከምንም በላይ ደግሞ በሁሉም በተለይ በኦርቶዶክስና በእስልምና የሀይማኖቱ መሪዎች (አባቶች) ሹመታቸው ከሚያመልኩት አምላክ እና ከምዕመናኖ የመነጨ ሳይሆን በመንግስት ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት የተፈፀመ ነው፡፡
2ኛ. የመንግስት አሠራር ለሕዝብ ግልፅ በሆነ መንገድ መከናወን አለበት፡፤ በሕገ መንግስት አንቀጽ 12 ንዕሱ አንቀፅ 1 ተደንግጎ የሚገኝ ነው፡፡ቢሆንም ከታችኛው የስልጣን እርከን ከሆነው ከቀበሌ ጀምሮ እስከላይኛው የመንግስት ባለስልጣናት አማከኝነት የሚከናወኑ የመንግስት አሰራሮች ግልፅነት እጅግ በጣም ጠባብ ነው፡፡በመሆኑም ህብረተሰብ በአገሩ ጉዳይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን በመንገስት አሠራር ላይ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አልተደረገም፡፡
በዚህም ምክንያት የመንግስት አሠራር ለሙሱና የተጋለጠ ነው፤ሙሱና በአሁን ወቅት በአገራችን ህጋዊ እስከመሆን ደርሷል፡፡በመሆኑም ማናኛውም የመንግስት ኃላፊ ኃላፊነቱን ወይም ስልጣኑን መሠረት አድርጎ ሲበድል እንጂ ለበደሉ ተጠያቂ ሲሆን አልታየም፡፡ስለዚህም የመንግስት አሠራር በየትኛውም ደረጃ ለህዝብ ግልፅ አይደለም ይህ ደግሞ የህገመንግስቱ ድንጋጌ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው፡፡
3ኛ. ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት አለው፡፡ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 14 ተፅፎ ይገኛል፡፡ነገር ግን የሰው ደህንነትን ለመጠበቅ የተቋቋመው የደህንነት መስሪያ ቤት በየደኑና በየጫካው የስንቱን ሰው ህይወት እንዳጠፋና የአካል ጉዳት እንዳደረስ የሚያውቀው ያውቀዋል፡፡ በተጨማሪ ይህ የነፃነት መብት ገዢው መንግስት በችሮታ ወይም በፍቃዱ የሰጠን እንጂ ሰው በመሆናችን ያገኘነው መብት እንዳልሆነ በሚያሳብቅ መልኩ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት በገዢው መንግስት መልካም ፍቃድ ላይ የተመሠረተ እስከሚመስል ደረስ ተደርሷል፡፡
4ኛ. ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት ፣ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብሩን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 18 ላይ ይገኛል፤ ይህ የህገመንግስት ድንጋጌ መሸራረፍ ሳይሆን መገርሰስ የሚጀምረው በህገመንግስቱ በተቋቋመው በህግ አስፈጻሚው አካል ነው፡፡
በመሆኑም ክብርን ለማወረድና ጭካኔን ለማሳየት የሰለጠኑ አሰቃዮችና ማሰቃያ ቦታዎች መኖራቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ነገሩን ለማነፃፀር እንዲረዳ  ፖለቲከኛ ወይም በህግ ጥላ ስር ያለ ሰውን ይቅርና ስታዲዮም እግር ኳስ ለመመልከት ወራፋ የሚጠብቅ በወረፋ ምክንያት ለተነሳ አለመግባባት ፖሊስ እንዴት አድርጎ እንደሚቀጠቅጥ ዱላውን የቀመሰ ያውቃል፡፡
5ኛ. በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚጠብቅ መልኩ የመያዝ እና ከሰዎች ወይም ከጠያቂዎቻቸው የመገናኘት መብት አላቸው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ አንቀፅ 21/1እና2 ተፅፎ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ ነፃ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች አያያዛቸው ክብርን ከመንካት አልፎ በህይወታቸው ላይ አደጋ የሚያስከትል ነው፡፡በተጨማሪ ከቤተሰብ፣ከወዳጅ መጠየቅ የማይሞከር ነገር ነው፤ የመጠየቅ እድል ያላቸው እስረኞች እድላቸው በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
6ኛ. ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? እርግጥ ነው ገብያውኑ መሰረት ያደረጉ መዝናኛ ላይ ያተኮሩ መፅሔትና ጋዜጣ ለቁጥር በዝተው ይሆናል፡፡ ግን ሁሉ ነገር በአገር ነው የሚያምረው! ታዲያ ስለ አገር በነፃ አሳብ የሚንሸራሸርበት መፅሔትና ጋዜጣ ምን ያኸል ነው ? ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡
7ኛ. ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ ሠላማዊ ሠልፍ እና ስብሰባ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 30/1 ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆን የቅርብ ጊዜ አይን ያወጣ የህገመንግስት ጥሰት ማቀረብ ይቻላል፡፡በሳውዑዲ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍና በደል ይቁም፣ይህንንም የፈፀሙ ለፍርድ ይቅረብ በማለት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው ሠላማዊ ሠልፍ በፖሊስ ዱላ እና እስራት ነው የተጠናቀቀው፡፡ በተጨማሪ በመንግስት እየታየ ያለው የአስተዳደር ብሉሹነት ለማመልከት እና ምላሽ ለማገኘት የተጠሩ የተለያዩ የተቃውሞ ሰልፎች እና ስብሰባዎች በመንግስት ቀጥተኛ ትእዛዝ ተከልክሏአል፡፡ሠላማዊ ሰልፍ ማድረግ እና አቤቱታ ማቅረብ መብት ነው! በማለት ክልከላውን ወደ ጎን በመተው አደባባይ ለመውጣት የሞከሩ ለእስርና ለድብደባ ተዳርገዋል፡፡በመሆኑም የተቃውሞ ሠልፍና ስብሰባ በማድረግ አቤቱታ በኢትዮጵያ ማድረግ የሞት ሽረት ትግልና ጥያቄ ከሆነ ሰንብቷል፡፡
8ኛ. የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግስት ባለስልጣን ሆነ አካል ተፅዕኖ ነጻ በመሆን በሙሉ ነፃነት ከህግ በስተቀር በሌላ ሁኔታ አይመሩም፡፡በማለት በህገመንግስቱ አንቀፅ 79 እና በተከታዮቹ ንዑስ አንቀፅ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ ዳኞች የመንግስት አስፈፃሚ አካል ከሆነው ነው ሹመታቸውን የሚያገኙት፡፡በመሆኑም ከመንግስት ጋር ቀጥተኛ ግኝኙነት ያላቸው የፍርድ ውሳኔዎች ምንያኽሉ በህግ እና በህሊና ላይ የተመሠረቱ ናቸው ? በተለይ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች የፍርድ ሂደታቸው ምን ይመስል ነበር ? እነዚህን እና መሰል ዳኝነቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በህገመንግስቱ የሰፈረው ነጻ ዳኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው፡፡
9ኛ. የሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የጎሳዎች ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ ይሆናል፡፡ ተብሎ በህገመንግስቱ አንቀፅ 87/1 ተደንግጎ ይታያል፡፡ነገር ግን በየድንበር እና በተልኮ ጭዳ ከሚሆነው ውጪ አብዛኛው የሠራዊቴ አባል እና አዛዥ የአንድ ጎሳ ስብስብ ነው፡፡ ስለዚህም ሠራዊቱ የማነው የኢትዮጵያ ወይስ ወደሚል ጥያቄ እያመራ ይገኛል፡፡
10ኛ. በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡
በመሆኑም እነዚህ እና መሰል የህገመንግስቱ ድንጋጌዎች ጥሰት ወይም በእነሱ ቋንቋ የመንድ ተግባር እየተፈፀመ ያለው በህገመንግስቱ በየወንዙ ዳር የሚማማለው ገዥው መንገስት ነው፡፡ ህገመንግስት የበላይ ህግ ነው፡፡ማንኛውም ህግ፣ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት ባለስልጣን አሰራር ከህገመንግስቱ የሚቃረነረ ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም ፡፡ የሚለው አንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 1 የገዥው መንግስት ደራሽ ዉሃ ጠራርጎ ወስዶታል፡፡ ስለዚህም የብሔሮ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የሚለውን መጠሪያ ስም በመስጠት ከበሮ ተይዞ የሚደለቅለት እና የሚከበረው ህገመንገስት መልሶ ካላስከበረ ፌሽታው እና ቀረርቶው ከምን የመነጨ ነው  ?
ይድነቃቸው ከበደ

ከሳውዲ ተመላሽ ዜጎች ንብረታቸው በጉምሩክ እንደተወሰደባቸው ተናገሩ

ህገወጥ ናችሁ ተብለው ከሳውዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያዊያን፤ ለበርካታ አመታት ለፍተን ያፈራነውን ንብረት ይዛችሁ መግባት አትችሉም ተብሎ ተነጥቀናል፡፡ 

radar_homeward_bound

የፍተሻ ሰራተኞች ሻንጣዎቻቸውን በመፈተሽ፣ ሞባይል ከአንድ በላይ ከያዙ ትርፉን በማስቀረት፣ አዳዲስ አልባሳት እና ኤሌክትሮኒክስ ቁሰቁሶች የተወሰኑትን ብቻ በመፍቀድ እና ያመጡትን ወርቆች ግራም በመቀነስ ንብረታቸውን እየወሰዱባቸው እንደሆነ ተመላሾቹ ገልፀዋል፡፡ መሃመድ አባመጫ የተባለ የሳኡዲ ተመላሽ፤ ከሳውዲ ስድስት ሻንጣ ይዞ መምጣቱን ገልፆ፤ ቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ ግን ከሁለት ሻንጣ በላይ ይዞ መግባት እንደማይችል፣ ከአምስት ሞባይሎችም ሁለቱ ብቻ እነደተፈቀደለት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ የሳውዲ መንግስት ከአንድ ኪሎ በላይ ወርቅ ይዛችሁ መውጣት አትችሉም የሚል መመሪያ ማሳለፉን የጠቆመው ተመላሹ፤ ንብረቱን እዚያው ጥሎ ለመመለስ መገደዱን ገልጿል፡፡ የሳኡዲ መንግስት እንኳን ከወርቅ በስተቀር ሌላ ንብረታቸውን ሁሉ ይዘው እንዲወጡ መፍቀዱን የገለፀው መሃመድ፤ በአገራቸው ንብረታቸውን እንዳያስገቡ መከልከላቸው እንዳሳዘነው ይናገራል፡፡

ኤሌክትሮኒክስና ለቤተሰቦቹ ያመጣውን ልብሶች ቀረጥ ከፍለህ ነው የምትወስደው በመባሉ፣ ለሁለት ቀን በስደት ተመላሾች በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ያለምንም ፍራሽና ልብስ ተኝቶ ንብረቱን ቢጠብቅም ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡ “ሳዑዲም እዚህም ሀገራችን ስንደርስ እየበደሉን ያሉት ሃበሾች ናቸው” ያለው መሃመድ፤ መንግስት በሚዲያ በተሟላና በተደላደለ መንገድ እንደሚቀበለን ቢገልፅም እዚህ የጠበቀን ግን ሌላ ነው ሲል ቅሬታውን ገልፆ “ሌላው ቢቀር እስካሁን ተመላሾቹን የሚያመላልሰው እንኳን የሳዑዲ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት አይደለም” ብሏል፡፡ ከሳኡዲ ካመጣችው ወርቅ ላይ ሃምሳ ግራሙን ብቻ እንደምትወስድ የተነገራት ተኪያ ሙሃመድን ያገኘናት በቁጭት መሬት ላይ እየተንከባለለች ነበር፡፡
ተኪያ እያለቀሰች እንደነገረችን፤ ለ14 ዓመት ሰርታ ከሶስት መቶ ሃምሳ ግራም በላይ ወርቅ እንዳጠራቀመች ገልፃ፤ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከሳውዲ እንድትወጣ ከመገደዷ በፊት ሙሉ ንብረቷን አስቀድማ ብትልክም እስካሁን እንዳልደረሰላት ትናገራለች፡፡ አሁንም፤ ከተመለሰች በኋላ የያዘቻቸውን ሻንጣዎች ለመውሰድ እንዳልቻለች የምትገልፀው ተኪያ፤ በፍተሻ ስም ሰራተኞቹ ሻንጣዋን በርብረው በማየት፣ ያመጣቻቸውን የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ሶስት ሞባይሎች መውሰዳቸው ሳይንስ፣ ሶስት መቶ ግራም የሚመዝን የወርቅ ንብረቷን እንዳታስገባ መከልከሏን በጩኸት ትናገራለች፡፡ ለምን ንብረቷን እንደከለከሏት ስትጠይቅም “እናንተ ነጋዴዎች ናችሁ፤ በስደተኞች ስም ያለቀረጥ ንብረት ለማስገባት ትፈልጋላችሁ” በማለት ሰራተኞቹ እንደመለሱላት ገልፃ፤ ጉዳዩን ለአለቆቻቸው ለማመልከት ብትፈልግም የሚያናግራት ሰው አለማግኘቷን ጠቁማለች፡፡ በዚሁ ስፍራ ያገኘናቸው በርካታ ተመላሾች፤ የንብረታቸው ጉዳይ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ። ንብረታቸውን ሳይዙ ወደቤተሰቦቻቸው ላለመቀላቀል በሚል የተሰበሰቡበት ካምፕ፣ ምንም ለማረፊያ የተመቻቸ አገልግሎት ባለመኖሩ መቸገራቸውንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት የሚሰጣቸውን 900 ብር፣ በትራንስፖርትና በስልክ አገልግሎት እንደሚጨርሱ አክለው ተናግረዋል፡፡
በርካቶች በእቃዎቻቸው መታገድ በመበሳጨታቸው ጭቅጭቅና አላስፈላጊ ውዝግብ ውስጥ ለመግባት መገደዳቸውን ተመላሾቹ ይናገራሉ፡፡ “ስንመጣ የሚሰጠንን ሊሴ ፓሴን አይተው ማስተናገድ ሲገባቸው እነሱ ግን ንብረታችንን እየወሰዱብን ነው” በማለት የሚናገሩት ተመላሽ ዜጎቹ፤ “ምናልባትም ንብረት የላቸውም ብለው አስበውን ይሆናል፤ ነገር ግን በርካታ አመታት ስንቆይ መቼም ባዶ እጃችንን አንመጣም” በማለት በምሬት ይናገራሉ፡፡ “ዛሬ እቃችንን የከለከሉን ነገ ምን ተስፋ ይዘን ነው ተደራጅታችሁ ስራ ስሩ ለሚሉን?” የሚሉት እነዚህ ተመላሾች፤ “በመንግስት ላይ አመኔታ የጣልነው ሳውዲ ድረስ በተወካዮቹ አማካኝነት መጥቶ ባናገረን መሰረት ነበር፤ ነገር ግን የተገባልን ቃል ታጥፏል” ይላሉ፡፡ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠቱ እና ለቤተሰብ መርዶ ባለመነገሩ፣ ለሚያውቋቸው ቤተሰቦች መርዶ ለመንገር ጭንቀት ላይ መሆናቸው ሌላ ችግራቸው እንደሆነ የተናገሩት ተመላሾች፤ አሁንም ቢሆን ሳውዲ ላይ ሃበሻዎችን በመኪና እየገጩ መግደል የሳውዲ ፖሊሶች የቀን ተቀን ስራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ታዲያ በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ አምልጠው የሚመለሱ ዜጐችን ንብረት መቀማት ምን የሚሉት ተግባር እንደሆነ አልገባንም፤ በማለት አማርረዋል-ተመላሾቹ፡፡ ምናልባትም የፖለቲካ ማራመጃ ሊያደርጉን ነው በማለትም ስጋታቸውን አንፀባርቀዋል፡፡
ተመላሾቹ የተሟላ መጠለያ ተዘጋጅቶላችኋል በተባለበት ቦታ ሳይቀር፣ መተኛ ሥፍራ እንኳን እንዳልተዘጋጀ ሲረዱ ተስፋ መቁረጣቸውን እና ንብረታቸውን እንዳያስገቡ ሲከለከሉ፣ ተመልሰው በህገወጥ መንገድ ለመሰደድ ሙከራ መጀመራቸውን ይገልፃሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ መልስ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸው፤ “ተመላሾቹ ስለንብረት የሚያነሱትን ጥያቄን በተመለከተ፤ እኛ ተመላሾች በሙሉ ንብረት እንደሌላቸው ነው የምናውቀው“ በማለት ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ከሳዑዲ የተመለሱ እንዳሉ ጠቁመው፤ በሳኡዲ መንግስት ጓዛችሁን ይዛችሁ እንዳትወጡ ተከልክላችኋል በመባላቸው፣ መጀመሪያውኑም ንብረት ይዘው ባለመምጣታቸው ነው፤ ብለዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች ከመደበኛ የአየር መንገዱ ተጓዦች እኩል እንደማይስተናገዱና ለብቻቸው ተጠብቀው እንደሚስተናገዱ ገልፀው፤ ምናልባት ከነዚህ ዜጎች ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ሌሎች ሰዎች ስለሚኖሩ እሱን ለማጣራት ንብረታቸው ይፈተሻል እንጂ ማንም የእነሱን ንብረት የሚወስድ እንደሌለ የተናገሩት አምባሳደሩ፤ እንኳን በሀገር ውስጥ የገባ ንብረት፣ ሳዑዲ ያለውንም የላባቸውን ውጤት ለማስመጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሟቾችን ቁጥር እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ አለመንገርን በተመለከተ አምባሳደሩ በሰጡት ምላሽ፣ አሁን ሙሉ በሙሉ ትኩረታችን በህይወት ያሉ፣ ንብረታቸውን ያጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ላይ ነው፤ ብለዋል፡፡ የሟቾቹን ቁጥር በተመለከተ ግን መንግስት ከገለፀው በኋላ፣ የተፈጠሩ ነገሮች መኖራቸውን አምነው፤ ነገር ግን ቁጥሩ ላይ ተመላሾች የሚሉትና አንዳንድ ሚዲያዎች የሚያወሩት ትክክል ሊሆን ቢችልም የተጣራ ነገር እስካላገኘን ድረስ የሞቱበትን ሁኔታ ለማወቅ ያስቸግራል፤ ብለዋል፡፡ የሳውዲ አየር መንገድ እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመመለሱ ሂደት ምንም አስተዋፅአ ለስደተኞቹ አላደረገም ለተባለው አምባሳደሩ መልስ ሲሰጡ፡- የሳውዲ አውሮፕላን የሚያመላልሰው እራሱ በማባረሩ ምክንያት ነው፤ ወጪውን የሚችለውም እራሱ ነው ብለዋል፡፡ addisadmas

ሚሚ ስብሃቱ ጠረጴዛ ምን ያደርግላታል?


mimi-sibehatuጠረጴዛ ከመመገቢያነት፣ለመጻፊያ ማስደገፊያነትና ከቁሳቁስ ማስቀመጫነት በተጨማሪ በዙሪያው በሚኮለኮሉት ወንበሮች የተነሳ ሰዎችን በአንድነት መሰብሰብ በመቻሉ የሐሳብ መንሸራሸሪያ መድረክ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ የሚቀመጡ ግለሰቦችና ቡድኖች በፊት ለፊታቸው በተዘረጋው ጠረጴዛ ላይ ሐሳባቸውን፣አመለካከታቸውንና አይዶሎጂያቸውን ያቀርባሉ፡፡የተጣሉ፣ልዩነት ያለባቸው ወገኖችም በጠረጴዛ ዙሪያ ቅራኔያቸውን ለማጥበብ ይደራደራሉ፡፡
ሚሚ ስብሃቱ ከቪኦኤ መልስ በታደለችው ዛሚ ራዲዩ ጣቢያ አማካኝነት ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ››የተባለ መርሃ ግብር ታዘጋጃለች፡፡በሚሚ ጠረጴዛ ዙሪያ እንዲታደሙ የሚፈቀድላቸው ወይም በቋሚነት በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ጋዜጠኝነታቸው‹‹በጠረጴዛው››የተወሰነ መሆኑም ድንቅ ይለኛል፡፡
ጋዜጠኞቹ ሚሚ ስታሽካካ አብረዋት የሚያሽካኩ የራሳቸው ሳቅ ወይም ለቅሶ የሌላቸው ‹‹እንገላበጥ››በማለት የሚጠይቁ ሁሌም ባለችው ላይ የሚጨምሩ መሆናቸውም ‹‹ጠረጴዛው››እውነት ከብበውታልን በማለት እንድጠይቅ ያደርገኛል፡፡
ሚሚ ዳዊት ከበደ መታሰር ይገባዋል ካለች ቀሪዎቹ የጠረጴዛው ታዳሚዎች‹‹እስካሁን አለመታሰሩ እንደሚገርማቸው ያክላሉ፣አንድነት ፓርቲ የግንቦት 7 ትርፍራፊን ለማግኘት ይሰራል ካለች አጃቢዎቿ ‹‹ለዚህ እኮ ነው የጸረ ሽብር አዋጁ ይሰረዝ የሚለው ይላሉ፡፡
ዛሬ አንድ ወዳጄ ደውሎ ሚሚን ስማት አለኝ፡፡ወሪያቸው ሚስ አና ጎሜዝን የተመለከተ ነበር ፡፡ሚሚ የስድብ መዝገበ ቃላቷን ጠረጴዛዋ ላይ ከፍታ ፖርቹጋላዊቷን የሰብዓዊ መብት ታጋይና የአውሮፓ ፓርላማ አባል ታወርድባታለች፡፡አና ሚሚን ባትሰማትም ሚሚ በተሳደበች ቁጥር ማንነቷን የምትገኝበትን ስብዕና የበለጠ እመለከት ነበር፡፡ማን ነበር ሰው አፉን ሲከፍት ሆዱ ይታያል ያለው፡፡
ሚሚ አና ጎሜዝ ወደ አገራችን እንድትገባ በመደረጓ ብዙ ኢትዮጵያዊያን አዝነዋል፡፡ብላለች የእርሷ ብዙ ስንት እንደሆነ ባይገባኝም፡፡አና ለሚዲያዎች በሰጧቸው ቃለ ምልልሶች መለስን መረር ባሉ ቃላቶች መግለጻቸው ሚሚን አንጨርጭሯታል፡፡እንዲህ በመናገሯ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ተቆጥተዋል ከማለትም አልተመለሰችም ‹‹መለስ መላጣ ብሎ ማንም ሊሰድበኝ ይችላል መላጣዬን ግን እንዲነካ አልፈቅድለትም››ማለታቸውን ሚሚ እንዴት እንደረሳቸው አልገባኝም፡፡አና መለስን ‹‹አጭበርባሪ ነበር››በማለት ገልጸውታል፡፡አያጭበረብርም የሚል ካለ አናን መሞገት እንጂ‹‹እንዴት ብሎ በጠረጴዛ ዙሪያ የስድብ መዓት ማዝነብ የሚቻል አይመስለኝም ፡፡
አና መለስን እንዲህ ያሉት ከመሬት ተነስተው አልነበረም፡፡ያው ምርጫ 2005ን ማስታወስ ብቻ ይበቃል፡፡እነ ሚሚ የመለስን የቲና ተርነር ዘፈን በማስታወስም ወይዘሮዋ ብርሃኑ ነጋ ጋር ስለነበራቸው ግኑኝነት ለመሳለቅ ሞክረዋል፡፡እንግዲህ አና በዘንድሮው የአዲስ አበባ አመጣጣቸው ደመቅ ያሉ ፎቶ ግራፎችን ከአባ ዱላ ገመደና ከተሾመ ቶጋ ጋር ተነስተው ተመልክተናል፡፡አና አባዱላን ወይም ተሾመን አፈቀሩ ወይስ ሁለቱ ሰዎች አናን ከብርሃኑ ነጠቁ?
እነሚሚ ይህንን ሊያነሱ አልቻሉም፡፡ከዚህ ይልቅ ተዘባዝበው አድማጮቻቸውን ተሰናበቱ፡፡እኔ ልጠይቅ በዛሚ ጠረጴዛ የሚሰባሰቡ ሰዎች አንድ አይነት ዘፈን የሚዘፍኑ ሚሚ ያለችውን እንደ በቀቀን የሚደግሙ እንደ ገደል ማሚቱ የሚያስተጋቡ ናቸው፡፡ታዲያ ጠረጴዛ ምን ያደርግላቸዋል፡፡ባዶ ቤት አይሻልም፡፡ለእስክስታውም ይመቻል ብዬ እኮ ነው፡፡
ከዳዊት ሰለሞን

tirsdag 3. desember 2013

ዜጋ አገሩን እንዲጠላና ተስፋ እንዲቆርጥ እያደረጉ ያሉ ችግሮች መፍትሔ ያላገኘ ችግር እየተባባሰ ሄዶ አገርንና ሕዝብን ለአደጋ ይዳርጋል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ በቅድሚያ መፍትሄ ማግኘት ያለበት የመንግስት አመራር እና ፖሊሲ ሊታለፍ የማይገባው ጉዳይ ነው:: ወያኔ ተሸክሜዋለሁ ከሚለው መንግስታዊ የህዝብ ሃላፊነት አንጻር ሲታል ለዜኦች እና ለሃገሪቱ ደንታ ቢስ በሆኑ ብድናዊ የማይናበቡ አመራሮች ታጥሮ ከፊቱ የማይፈታው ከባድ አደጋ በራሱ እና በሃገኢቱ ላይ ጋርጧል::በሃገራችን ውስጥ ጠንካራ እና የጋራ የሆነ ንቁ መንግስት አለመኖሩ ህዝቦች ነገን በጭለማ እንዲያማትሩ እያደረገ ሲሆን በፖለቲካ ዱላ እየታሸ ያለው ህዝብ በኑር ውድነት እየተገረፈ ያለው ህዝብ ከአደጋ ራሱን ለማዳን እየተራወተ እየታገለ ይገኛል::

የወያኔ ገዢዎች ሃገርና ሕዝብን ሳያወያዩ እና ሳያማክሩ በሚፈጥሩት የሰነድ እና የጥናት የእቅድ ጋጋታ የሃገሪቱን ኢኮኖሚ መቃብር ውስጥ ከመክተታቸውም አልፈው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ራሳቸው የፈጠሯቸው ፕሮጀክቶች በገንዘብ እጥረት ምክንያት እየቆሙ ሲሆን የፖለቲካ ጡዘት በወሕኒ እንዲገደብ መደረጉ የሃይማኖት ጥያቄዎች መፍትሄ አለማግኘታቸው የሰው ልጅ መብቶች ሕጋዊ መሰረት አለመያዛቸው እንዲህና የመሳሰሉት ጉዳዮች መፍትሄ ስላልተሰጣቸው ተስፋፍተው ሃገሪቱን አደጋ ውስጥ መንግስት ነኝ ባዩንም አጣብቂኝ ውስጥ ከተውታል::

ገዢው ፓርቲ ውስጣዊ አንድነቱ ተናግቶ በሃገር አመራር ላይ በአመራሮቹ መካከል የተፈጠረው አለመናበብ እናም መራራቅ በሃገሪቱ እየተስፋፋ ለመጣው ችግር ዋነኛ መንስኤ ከመሆኑም በላይ የህዝብ አካል ነኝ የሚል ዝግጁነት ከነኣካቴው ጠፍቷል::የገዢው ፓርቲ ሰዎች በሙስና ተጨማልቀዋል::ይህ ሙስና ከመስፋፋቱ በፊት ምንም አይነት እርምጃ ሲወሰድ አይታይም የሙስና ምንጩን ማድረቅ ሳይሆን የተያዘው በፓርቲ ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ባላንጣዎችን እና ወዳጆቻቸውን መንከስ አስመስሎታል:: ከሙስና አንዱ አካል የሆነው የፖለቲካ ሙስናም በአመራሮቹ ውስጥ ተስፋፍቶ የህዝብ ጩኸት ሰሚ አቷል::በተለያዩ መስኮች የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ሙስናዎች እንደአዲስ እየተፈጠሩ ነው:;ይህ አደገኛ አደጋ መፍትሄ ካልተበጀለት....
የወያኔው ጁንታ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ እጥረት አለበት የሃገሪቱ በጀት ጸደቀ ለዚህ ፕሮጀክት ይህን ያህል ተመደበ እየተባለ በቃላት ጣፍጦ ቢወራም ተግባር ላይ ግን ተመደበ የተባለውን ለመልቀቅ ከባድ ፈተናዎች ውስጥ ገብቷል::የበጀት አፈጻጸም እንዳይኖር ከባድ እንቅፋቶች እየገጠሙ ነው የባንጎች እንቅስቃሴ ከመድከሙም በላይ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ከባድ እና የማይፈታ የገንዘብ ግሽበት እና መፍትሄ ተብለው የሚወሰዱ ውሳኔዎች ወያኔን ናላውን አዙሮታል::

ህዝቡ አቤቱታውን የሚያሰማበት አካል የለም:; መልካም አስተዳደር ፖለቲካን የተመረኮዘ እንጂ ህዝባዊነትን ያቀፈ አይደለም የመንግስት ባለስልጣናት እና የህዝብ አገልጋዮች በፓርቲ ስብሰባ ተጠምደው እለት ከእለት የህዝኡን አቤቱአይደለም የቤተሰቦቻቸውን ፍቅር እና እንክብካበ ሊያስተናግዱ አልቻሉም::የፓርቲ ስራ እና የመንግስት አገልግሎች በጋራ መማከሉ አለመለየቱ ከባድ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየፈጠሩ ናቸው ይህ ደግሞ የገዢው ፓርቲ አደገኛ አካሄድ የፈጠረው አደጋ ነው:: ...የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች መፈታት ሃገርን ከአደጋ ይታደጋታል ሰላምንም ይሰጣታል::

በአሁን ሰአት ከበፊቱ በባሰ መልኩ ከፍተኛ የተማረ የሰው ሃይል እንዲሁም የሰለጠነው በተጨማሪም ከስደት ተመላሹ ዜጋ በስራ አጥነት ተወጥሮ ስለሚገኝ የስራ እድሎች እንዴት እንደሚፈጥር ወያኔን ግራ ገብቶታል:: ዜጎች በሃገራቸው የሚገባቸውን መብት ማግኘት ከጀመሩ እና ባወጡት ህግ መገዛት ከቻሉ እንዲሁም እያንዳንዱ ዜጋ በሃገሩ እንዲያገባው ተደርጎ ከተገራ እና እኔ አውቅልሃለሁ ማለት ከቆመ በተጨማሪም ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ተደርገው በሃሳብ አማራኝ ላይ ለሃገር የሚበጀው ከተሰራ ሁላችንም በነጻነት መኖር እንደምንችል ማረጋገጥ እወዳለሁ::


ምንሊክ ሳልሳዊ

ESAT Special Mesay With Dr Berhanu Nega Dec 02, 2013


ESAT DC Daily 2 Dec 2013


የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካ


አውሮፕላኑ ቅዳሜ ጠዋት ሶስት ሰዓት ላይ ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ደርሶ ከተርሚናሉ ስወጣ፣ ተጠራጥሬ ሰዓቴን ተመለከትኩ፤ የድሬ የጠዋት ፀሐይ ከተለመደው ለእናት ሀገር ሲባል!›ን እየዘመሩ ወራሪውን የሶማሊያ ወታደር የኢትዮጵያ ምድር ግዛቱ ሳይሆን፣ መቀበሪያው ማድረጋቸውን ታሪክ መዝግቦታል፡፡ንዳዷ ጋር የአዲስ አበባን የቀትር መራራ ፀሀይን ታስከነዳለች፤ እናም አጥበርባሪ ጨረሯን ያለምህረት ስትለቅብኝ፣ ጓደኛዬ መኪና ይዞ እቦታው እስኪደርስ መጠበቁ በገዛ ፍቃድ መለብለብ ስለመሰለኝ፣ በቀጥታ ከተደረደሩት ታክሲዎች አንዱን ይዤ ወደ ከዚራ አመራሁ፤ ድሬ የሄድኩት በዋናነት ከማህበራዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምክንያት በመሆኑ ሊቀበለኝ የተዘጋጀውን
ጓደኛዬን ደውዬ ከማውቃቸው የአንዱን ሆቴል ስም ጠቅሼ እዚያ እንድንገናኝ ነገርኩት፡፡
የሆቴሉ ፍተሻ ከወትሮው ጠንከር፣ ጠጠር ያለ በመሆኑ ትዕግስትን ይፈትናል፡፡ እንዲህም ሆኖ ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ማረፊያ ክፍሎች በሙሉ መያዛቸው ተነግሮን ቀኝ ኋላ ለመዞር ተገደድን፤ ይሄኔም ነው የጓደኛዬ ፊት ልውጥውጥ ሲል ያስተዋልኩት፤ ጭንቅላቴን በማነቃነቅ በምልክት ምን እንደተፈጠረ ጠየኩት፤ ለአፍታ አመንትቶ ከፊት ለፊታችን በግምት አስር ሜትር ርቀት ላይ ወደቆሙ ሁለት ሰዎች ጠቆመኝ፤ ልብ ብዬ አየኋቸው፤ ሁለቱንም ከዚህ ቀደም አይቻቸው አላውቅም፤ ደግሞም በዙሪያችን ከሚርመሰመሱ ሰዎች የተለየ ምንም አይነት ሁኔታ ላስተውልባቸው አልቻልኩም፤ እናም ወደ ጓደኛዬ ዞሬ በግርታ ግንባሬን ቋጥሬ ጥያቄ በተሞላ ዓይን አተኮርኩበት፤ ጓደኛዬም ከሁኔታዬ እንዳልገባኝ ተረድቶ ከሹክሹክታም ዝቅ ባለ ድምፅ ‹‹ደህንነቶች ናቸው፣ እየተከታተሉህ ነው›› አለኝ፤ ቢሆኑስ ታዲያ!? በግዴለሽነት ትከሻዬን እየሰበቅሁ ‹‹ለራሳቸው ጉዳይ መጥተው ሊሆን ይችላል›› ብዬው ወደ ሌላ ሆቴል አቀናን፤ እዛም የተለቀቀ ክፍል አለመኖሩ ተነግሮን ፊታችንን ከእንግዳ መቀበያው ‹‹ዴስክ›› ዘወር ስናደርግ እነዛ ‹ደህንንቶች› ቆመው ተመለከትኳቸው፡፡ አሁን ከልምዴ በመነሳት ክትትል ሊሆን እንደሚችል ለማመን በተቃረበ ጥርጣሬ ተውጬ ሌላ ሆቴል ደርሰን ክፍል ጠየቅን፤ በለስ ቀናንና የሆቴሉን መስፈርት አሟልቼ ሳበቃ ጓደኛዬን ቡና ቤቱ ውስጥ እንዲጠብቀኝ አድርጌ፣ ክፍሉን ከተረከብኩ በኋላ ሻንጣዬን አስቀምጬ፣ ገላዬን ተለቃልቄ፣ ልብስ ቀይሬ ደረጃውን መውረድ እንደጀመርኩ ከሰዎቹ ጋር ፊት ለፊት ተገጣጠምኩ፡፡ የጭንቅላት ሰላምታ ሰጥቼ አለፍኳቸው፤ ምላሽ የለም፤ ፈገግ አልኩ፡፡ ከወዲሁ የሰሞኑ ምስራቅ ኢትዮጵያ አክራሞቴ ምን ሊመስል እንደሚችል አሰብኩና፣ በልጅነቴ ከሰፈር ማቲዎች ጋር የምንጫወተውን የአኩኩሉ ድብብቆሽ አስታውሼ፣ በድጋሚ ለራሴ ፈገግኩ፡፡
ገና ከአዲስ አበባ ስነሳ ማህበራዊ ጉዳዬን ስጨርስ የድሬዳዋ፣ ሐረር እና ሶማሌ ክልልን ወቅታዊ የፖለቲካ ትኩሳት ለማዳመጥ ለተጨማሪ ስድስት ቀናት የሚያቆይ ፕሮግራም አስቀድሜ ይዤ ነበር፤ ከአራት ቀን ቆይታ በኋላም ቀጥታ ወደዚሁ ስራዬ ነበር የገባሁት፡፡ ለጉዳዩ ትኩረት እንድሰጥ ያደረገኝ በቅርቡ ሐረር ከተማ ውስጥ በተከበረው ‹‹የዓለም የመቻቻል ቀን›› ላይ በክልሉ የተንሰራፋው መድልዎና የሐብሊ ተፅዕኖ ተደብቆ፣ ፍትሐዊ አስተዳደር የሰፈነ ለማስመሰል መሞከሩ፤ እንዲሁም ህዳር 29 ቀን በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅጅጋ (ጅግጅጋ) የሚከበረውን ‹ስምንተኛው የብሔር ብሔረሰብ ቀን›ን አስመልክቶ አካባቢውን ከዋጠው ስጋት በተቃራኒው መንግስት እየነዛ ያለው የሀሰት ፕሮፓጋንዳን ከተጨባጩ እውነታ ጋር ለመፈተሽ ፍላጎት አድሮብኝ ነው፡፡
ፊታችሁን ወደ ምስራቅ…
ምስራቅ ኢትዮጵያ ከሀገሪቱ የ3ሺ ዓመት ታሪክ ዕኩሌታውን ሰላምና መረጋጋት የተሳነው ከመሆኑም በላይ፣ ለማዕከላዊ መንግስት የስጋት ምንጭ ሆኖ ነው ዛሬ ድረስ የቀጠለው፡፡ ከአቶማን ተርኪሽ ወታደሮች እስከ አል-ሸባብ ሰርጎ ገቦች ድረስ መተላለፊያ ‹‹ኮሪደር›› ሆኖ አገልግሏል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ ሶማሊያውያን የዘር ግንድ ከጐረቤት ሀገራት ሶማሊያና ጅቡቲ ጋር የሚተሳሰር መሆኑና የሃይማኖትና የኢኮኖሚ ምንጭም ተመሳሳይነት አካባቢውን በበቂ ደረጃ ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እንዳደረገው የፖለቲካ ተንታኞች ያምናሉ፤ ነዋሪዎቹ በቀላሉ ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው እየተዘዋወሩ የሚኖሩ መሆናቸውም ሌላው ችግር እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ ቅኝ ገዥዎቹ የአውሮፓ ሀገራት በበኩላቸው አካባቢውን ‹ፍሬንች ሶማሌ ላንድ›፣ ‹ብሪታኒያ ሶማሌ ላንድ› እና ‹ኢታሊያ ሶማሌ ላንድ› በሚል ከፋፍለው ማስተዳደራቸው፣ ከሶማሊያ ነፃነትም በኋላ የሞቃዲሾን ቤተ-መንግስት የተቆጣጠሩ ገዢዎች ‹ታላቋን ሶማሊያ እንመሰርታለን› በሚል ቀቢፀ ተስፋ ከአንድም ሶስቴ የኢትዮጵያን ወሰን ተሻግረው የኃይል ወረራ መፈፀማቸው የአካባቢውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶት ነበር፤ ከዚያም ባሻገር የዚያድባሬ ሶማሊያ መፈራረስም የቀጠናውን ሠላምና ፀጥታ ከድጡ ወደ ማጡ አድርጎታል፡፡
በዚህ ሁሉ ከባቢያዊ ውጥረት እየታመሰ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ በአንድነት በሐረርጌ ክፍለ ሀገር ስር ሲተዳደር የቆየው የምስራቁ የሀገራችን ክፍል፣ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ ባነበረው ‹‹ፌደራሊዝም›› በሶስት ሊከፈል ችሏል፤ ‹‹የሶማሌ እና ሐረር ክልል›› እንዲሁም ‹‹የድሬዳዋ አስተዳደር›› በሚል፡፡ ይህ ሁኔታም ከዚህ ቀደም በውጭ ተፅዕኖ ይተራመስ የነበረውን ‹ጂኦ-ፖለቲክስ› ብሔር  ተኮር ለሆነ ተጨማሪ አዲስ ቁርቁስ አጋለጠው፡፡ በአናቱም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ ኦጋዴን፣ ጎዴ፣ ደጋሀቡር፣ ቀለፎን የመሳሰሉ ከተሞች ክልሉን ‹እንገነጥላለን› የሚሉት የኦጋዴን ብሔራዊ ግንባር ታጣቂዎች መርመስመሻ መሆናቸው አካባቢውን የስጋት ቀጠና አድርጎታል፤ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ድሬዳዋ ላይ ያነጋገርኳቸውና በሽግግር መንግስቱ ወቅት የአስተዳደሩ አባል የነበሩ አቶ ኡስማን (ለዚህ ፅሁፍ ስማቸው የተቀየረ) ‹‹የዚህ ሁሉ ተጠያቂ ለጣልቃ ገብነቱ ያልተመቹትን የአካባቢው ልሂቃን ‹ለወረራ የመጡ የዚያድባሬ መኮንኖች› እያለ አሸማቅቆ ከፖለቲካው ገፍቶ በማስወጣት ክልሉን ዛሬ ላለው ደካማ አስተዳደር የዳረገው ኢህአዴግ ነው›› ይላሉ፡፡ በግልባጩ የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ካሳ ተክለብርሃን የተገፉት ሰዎች ኢትዮጵያዊ አለመሆናቸውን ለ‹‹ዘመን›› መፅሄት የገለፀው እንዲህ በማለት ነበር፡-
‹‹ሶማሊያ የፈራረሰበት ወቅት ስለነበር በጣም ትላልቅ የሶማሊያ ተፈናቃዮች የሰፈሩባቸው ካምፖች ነበሩ፡፡ እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ አንዱ የስደተኞች ካምፕ የነበረባት አገር ነበረች፡፡ በተለይ አርትሼክ አካባቢና ሌሎች አካባቢዎችም ትልልቅ ካምፖች ነበሩ፡፡ በዚህ ጊዜ የመጡ የዚያኛው ሶማሊያ መኮንኖች፣ ሲቪል ሰራተኞች ኢንጂነሮችና ፓይለቶች ነበሩ፤ በአካል ያገኘናቸው የምናውቃቸው እነዚህ ከኢትዮጵያ ሶማሌ ጋር የሚለያቸው ነገር ስላልነበረ በአብዛኛው በስደተኛነት ከመጡ በኋላ የአካባቢውን የፖለቲካ ስልጣኑንም ያደራጁት እነሱ ነበሩ፡፡ አንዱ ትዝ የሚለኝ ይሄ ነው፡፡ ይሄንን የኢህአዴግ ሰራዊትና ከላይ የሄደው የኢትዮጵያ ሰራዊት ሊለየው አይችልም ብቻ ሳይሆን ያ የመጣውን እንዳለ የሚያቅፍ ሁኔታ ነው የነበረው በአካባቢው፡፡ ስለዚህ ለረጅም ጊዜ ያ ኃይል ነው እንግዲህ አዲስ በተፈጠረው አጋጣሚ የታላቋ ሶማሊያን አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሶማሊያ ላይ ለመዝራት ትልቅ ጥረት ያደረገው››
ይህ ክርክር በራሱ ኢህአዴግ ‹‹ፊታችሁን ወደተረጋጋችው ምስራቅ ኢትዮጵያ (ሶማሊ ክልል) መልሱ›› ያለበት አውድ የተለመደው የቅጥፈት ፕሮፓጋንዳ እንጂ አካባቢው የጦርነት ወረዳን ያህል የሚያሰጋ መሆኑን ያመላክታል ፡፡ እናም ከአርቲስቶች እና ጋዜጠኞች እስከ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ፊት-አውራሪነት የተካሄደው የጉብኝት ፕሮግራም፣ መንግስት ምንም እንኳ የህዝቦችን አንድነት ‹የማጥበቅ ዕቅድ› የሚል የዳቦ ስም ቢሰጠውም፣ ‹ሶማሌ ክልል ፍፁም ሰላም ነው› የሚል የሀሰት ፕሮፓጋንዳን ለመንዛት መሆኑን ለመረዳት በአካባቢው ያለውን የፀጥታ አጠባበቅ ብቻ መመልከቱ በቂ ይመስለኛል፡፡
የቦምባስ ዕገታ
ዘንድሮ ለስምንተኛ ጊዜ ‹‹ሕገ-መንግስታችን ለህዳሴያችን›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረው ‹‹የብሔር ብሔረሰቦች ቀን›› በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅጅጋ በመሆኑ በአካባቢው ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት ለመለካት ረቡዕ ህዳር 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ወፍ ጭጭ ሳይል ነበር ድሬዳዋን ለቅቄ ወደ ሐረር ጉዞዬን የተያያዝኩት፡፡ ይህንን ሰዓት የመረጥኩት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አዲስ አበባ ላይ እንኳ ጋብ እየለ የመጣውን የደህንነት ሰራተኞች ክትትል ድሬዳዋ ላይ በየደረስኩበት ሲያንዣብብብኝ፣ በማስተዋሌ፣ ምናልባት ከዕይታ ውጪ መንቀሳቀስ ብችል በሚል እሳቤ ነበር፡፡ መኪናው ከአንድ ቀን በፊት የተከራየሁትና ድሬ ውስጥ ያልተጠቀምኩበት በመሆኑ፣ በስጋት የሚንጠውን የደንገጎ አቀበትም ሆነ ጥንታዊቷን ሐረር ከተማ አቋርጠን እስክናልፍ አንዳች ችግር አላጋጠመንም፡፡ ይሁንና ከሐረር በግምት 80 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በሶማሊያ ክልል የምትገኘው ቦምባስ ከተማ ደርሰን ጥቂት እንደተጓዝን፣ መኪናውን ዳር አስይዞ እንዲያቆም አንድ የትራፊክ ፖሊስ ለሹፌሩ የእጅ ምልክት አሳየው፤ ይሄኔም ነው ድሬ ላይ እንደ ተሰወርኩባቸው እርግጠኛ ሆኜ በልቤ ከሳቅኩባቸው ሁለቱ ሰላዮቼ ጋር ፊት ለፊት የተፋጠጥነው፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ስሜን ጠርተው አነጋገሩኝ፤ እኔም ከምንም ነገር በፊት መታወቂያቸውን እንዲያሳዩኝ ጠየቅኩ፤ ሳያቅማሙ አሳዩኝ፤ ወዲያውኑም የአፍ መፍቻ ቋንቋው አማርኛ እንዳልሆነ የአነጋገር ዘዬው በግልፅ የሚያስታውቀው አንደኛው የደህንነት አባል፣ ከዚህ በላይ ጉዞውን መቀጠል እንደማልችልና በቀጥታ ወደ ድሬዳዋ መመለሱ እንደሚጠቅመኝ ሊነግረኝ ሞከረ፡፡ ከመገረሜ ብዛት ንግግሩን ለመረዳት ጥቂት ሰከንዶች ፈጅተውብኝ ነበር፡፡ መቼም ይህ ሰው ቀልደኛ መሆን አለበት! አለዛ በገዛ ሀገሬ የት ድረስ መሄድ ወይንም የት ቦታ ጉዞዬን መግታት እንዳለብኝ ሊወስንልኝ ባልደፈረ ነበር፤ ሆኖም ንዴቴን ዋጥ አድርጌ ምን ማለት እንደፈለገ እንዲያስረዳኝ በትህትና ጠየኩት… ይኼኔ ጓደኛው ጣልቃ ገባና ወደ ጅግጅጋ ለመሄድ ማሰቤን እንደደረሱበትና ወደ ከተማው እንድገባ እንደማይፈቅዱልኝ ቆጣና ኮስተር ብሎ አሳወቀኝ፡፡ እኔም ፈርጠም ብዬ እዚህ ድረስ መጥቼ ጅጅጋ ሳልደርስ እንደማልመለስ ቁርጡን ነገርኳቸው፡፡ ቃለ-ምልልሱ እየከረረ ሲሄድ ማስፈራራቱን ወደ ሹፌሩ አዞሩትና በብርቱ ያዋክቡት ያዙ፤ ይህ ድርጊታቸው ያልጠበቅኩት በመሆኑና የሹፌሩንም ምላሽ አለማወቄ መጠነኛ ድንጋጤ አጫረብኝ፡፡ እንደገመትኩትም ሁኔታውን በፍርሃት ተውጦ ይከታተል የነበረው ሹፌር ትንሽ እንኳ ሳያንገራግር መኪናውን ቆስቁሶ ወደ ሐረር አዞረው፡፡
‹‹ምን ሆነሃል?›› አልኩት በንዴት ጮኽ ብዬ፡፡
‹‹ወንድሜ እኔ ቤተሰብ የማስተዳድር ሰው ነኝ፡፡››

 

(ተመስገን ደሳለኝ)

ደግሞ ካሁኑ ዱለታው 2007 ምርጫ


አዎን አውቃለሁ፣ የምን ምርጫ ነው ትሉ ይሆናል፡ ይህም የኔም ጥያቄ ነው የእናንተ ብቻ ሳይሆን። የህውሃት/ወያኔ አገዛዝ እስካለ ድረስ በኢትዮጵያ ዳግም ትክክለኛ የሆነ ምርጫ
normal_904604ሊደረግ እንደማይችልና እንደማይኖር ብዙዎች የተነበዩት ነው። የሕዝብን ድምፅ አክብሮ በተሸናፊነት አምኖ ወያኔ ሥልጣኑን የመልቀቁ ጉዳይ ያከተመለት ይመስላል።
ህውሃት/ወያኔ አሁንም ስለምርጫው በሰፊው በማውራት ላይ ይገኛል፡ ሕዝብን በእህልና በምግብ አቅርቦት፡ በሥራ እድልና በመሳሰሉት እንደ ቀብድ በማስያዝ፡ በፓርቲው ስር ካልታቀፉ በሐገሪቱ ውስጥ ሊያገኟቸውና ሊጠቀሙባቸው የሚገባቸውን ሰብዓዊ መብቶች በመግፈፍ በውዴታ ሳይሆን በግዴታ የፓርቲውን የአባልነት ፎርም በማስሞላት ላይ ይገኛል። በቀደመው ምርጫ ድምጻቸውን ለተቃዋሚዎች የሰጡትን ግለሰቦች ከስራቸው እንዲባረሩ ወይም ሐገር ለቀው እንዲወጡ ለመጪውም ምርጫ እንቅፋት የማይሆኑበትን መንገድ በመቀየስ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል፡
ለማንኛውም ባለፈው የክልል ምርጫዎች እንደተደረገው አሁንም ምርጫው የሚካሄደው ወያኔ ከራሱ ከወያኔ ጋር ይሆናል እንጂ በዚህ ሁካታና የመብት መጣስ በሰፊው በተንሰራፋበት ሁኔታ ጠንካራ ተቃዋሚ ገብቶ ሥነሥርዓት ባለው ሁኔታ ምርጫ ይካሄዳል ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው። ለዚህም ነው 2002 ምርጫ ሲሉን የምን ምርጫ የሚለው ጥያቄ ሲያስተጋባ የምንሰማው።
እውነት ግን የምን ምርጫ ከአሁን በኋላ?

ኢትዮጵያ ”ብሔር ብሄረሰብ” እያለች እንድትዘምር ሲፈረድባት ጎረቤቶቿ ግን በብሄር ስም የፖለቲካ ድርጅት መመስረትን በሕግ ከልክለው በአንድ ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ላይ ደረሱ


ኢትዮጵያ ያረጀ ያፈጀውን የማርክሲስት አስተሳሰብ ”ብሔር ብሄረሰብ” ርዕዮት እንድትዘምር ተፈርዶበታል።ህዳር 29 ቀን ጅጅጋ ላይ የቀለጠ ድግስ ተዘጋጅቷል።የእዚህ አይነት ዝግጅት commoncurrበኢትዮጵያ ወጣቶች መካከል ለምሳሌ በትምህርት ቤቶች መካከል የሚደረግ ከፖለቲካዊ ይዘት የራቀ ግን ወጣቶች የሚቀራረቡበት መልክ ቢኖረው ብዙ ፍሬ ባፈራ ነበር።የኢህአዲግ ዝግጅት ግን ኢትዮጵያውያን አንድ የሚያደርጋቸው እልፍ ነገሮችን ማውሳት ትቶ የሚለያዩበት ነገር እየተነቀሰ የሚነገርበት መርሃ ግበር መሆኑ ነው አሳዛኙ ነገር።
ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ይሁን እንጂ ጎረቤቶቻችን ግን በሀገራቸው በብሄር ስም የፖለቲካ ድርጅት መመስረትን በሕግ ከልክለው በአንድ ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ላይ ደረሱ ።ቅዳሜ ህዳር 21/2006 ዓም የኬንያ፣ዩጋንዳ፣ታንዛንያ፣ቡሩንዲ እና ሩዋንዳ መሪዎች በዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ ተገናኝተው በአስር ዓመት ውስጥ የጋራ መገበያያ ገንዘብ እንዲኖራቸው የፕሮቶኮል ስምምነት ተፈራርመዋል። ይህ ማለት ኢትዮጵያን የሚቀናቀን ትልቅ ገበያ እንደሚፈጥሩ ይታመናል።ኢትዮጵያ በእዚህ ጊዜ ቢያንስ በታዛቢነት አለዝያም ከደቡብ ሱዳን፣ጅቡቲ፣ሱማልያ ወዘተ ጋር የጋራ ገበያ የምትፈጥርበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባት ነበር።ከእዚህ ይልቅ ”ምኑ ቀርቶብኝ በወጉ በኮነነኝ” እንደሚባለው የጎረቤት የጋራ ገበያ ቀርቶ ጠንካራ ሃገራዊ አንድነት እንዳትፈጥር በብሄር እንድታስብ ተፈርዶባታል።ህዳር 29 በቴሌቭዥን እያዘፈነች እበላ ባይ አፈጮሌ ካድሬዎቿ ስሽሞነሞኑ ማየት የሰሞኑ አሳዛኝ ድርጊት ነው። ጉዳያችን

 | 

mandag 2. desember 2013

ESAT Human Rights Ethiopian Prisoners in Yeman Sena Nov 30 2013


ESAT Daily News Amsterdam Dec 02 2013 Ethiopia


ሰበር ዜና፣ ግንቦት 7 ወያኔ ላቀረበው “እንደራደር” ጥያቄ መልስ ሰጠ

የወያኔ አገዛዝ በመልዕክተኞቹ በኩል ላቀረበው የ“እንደራደር” ጥያቄ ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ምላሽ

ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የገነባዉ ሥርዓት በከፍተኛ ችግሮች የተወጠረ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመሪው ሞት በወያኔ መሀል ያስከተለው ቀውስ፤ የሕዝብ ሁለገብ ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበት መሄድ የፈጠረበት ስጋት እና ምርጫ በደረሰ ቁጥር የሚደርስበት ጭንቀት መጨመር ተደማምረው ውጥረቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እያደረሱት መሆኑን የሚያሳዩ በቂ ምልክቶች አሉ። የእስካሁኑ ተሞክሮዓችን እንደሚያሳየው ወያኔ ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ የሚገዛ መሆኑን ነው። ሰሞኑን በወያኔ አገዛዝ መልዕክተኞች በኩል የደረሰንን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄያችን በዋናነት ያየው ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ መሆኑን ነው።

ኢህአዴግ/ህወሃት ከግንቦት 7 ጋር ለመደራደር ጥያቄ አቀረበ


እንደ ኢሳት (የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን) ዘገባ ከሆነ “ኢህአዴግ መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት ከግንቦት ሰባት ለፍትህና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር ለመደራደር ጥያቄ አቀረቧል።
የኢሳት ዜና አገልግሎት በአጭር ሰበር ዜና ዘገባው እንዳለው ማምሻውን የግንቦት ሰባትን አመራሮች መልስ ይዞ ብቅ ይላል።
ይህ በዚህ እንዳለ የኢሳትን ሰበር ዜናን ተከትሎ በማህበራዊ መገናኛ መረቦች ኢትዮጵያውያን አስተያየቶችን በመስጠት ላይ ይገኛሉ…
Ginbot 7 logo

søndag 1. desember 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ኢ/ር ይልቃል በጀርመን- በስዊዘርላንድ – በሆላንድ – በዋሽንግተን ዲሲ ውይይት ያደርጋሉ

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ኢ/ር ይልቃል በጀርመን- በስዊዘርላንድ – በሆላንድ – በዋሽንግተን ዲሲ ውይይት ያደርጋሉ
blue-party-ethiopiaየሰማያዊ ፓርቲ ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት የአውሮፓና የሰሜን አሜሪካ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል። ትላንት ኖቨምበር 29 ጀርመን ፍራንክፈርት የገቡት ኢ/ር ይልቃል በመጪዎቹ ቀናት በአውሮፓ ከተሞች ተከታታይ የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ አስተባባሪ ኮሚቴው በተለይ ለኢ.ኤም.ኤፍ አስታውቋል።
ለጊዜው በደረሰን የስራ ሰሌዳ መሰረት :-
– ቅዳሜ ኖቬምበር 30 በጀርመን ኑረንበርግ ከኢትዮጵያኖች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
– ሰኞ ዲሴምበር 2 በፍራንክፈርት የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
– ዲሴምበር 5 ጄኔቭ ስዊዘርላንድ የሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ይሳተፋሉ።
– ቅዳሜ ዲሴምበር 7 በሆላንድ ህዝባዊ ውይይት ያደርጋሉ።
ከአውሮፓ ቆይታቸው በኋላ ወደ ዋሺንግተን ዲሲ በመጓዝ በዲሴምበር 30 አርሊንግተን በተዘጋጀው ስብሰባ ከፕ/ር አል ማርያም ጋር ንግግር ያደርጋ

Saudi Arabia: Labor Crackdown Violence (Human Rights Watch)


November 30, 2013
Ethiopian Workers Allege Attacks, Poor Detention Conditions
(Beirut) –  Ethiopian migrant workers have been the victims of physical assaults, some of them fatal, inSaudi Arabia following a government crackdown on foreign workers. Many workers seeking to return home are being held in makeshift detention centers without adequate food or shelter.
Human Rights Watch spoke to five Ethiopian migrant workers in Saudi Arabia. Four Ethiopians in Riyadh told Human Rights Watch that the attacks began after November 4, 2013, when authorities resumed a campaign to arrest foreign workers who they claim are violating labor laws. Security forces have arrested or deported tens of thousands of workers. Saudi officials and state-controlled media have said that migrant workers have also been responsible for violence, including attacks on Saudi citizens, in the wake of the crackdown.

lørdag 30. november 2013

Ana Gmes Speaks: Addis Standard’s exclusive interview

Ana Gomez


 ADDISSTANDARD   

Ana Gomes is coordinator and spokesperson of the foreign affairs committee for her political group, the Social-Democrat. With 200 members the Social-Democrat is the second largest group within the European Parliament. For Ethiopia and Ethiopians though Ana Gomes is best remembered for her role as the leader of the EU election observers’ team during the 2005 crisis-induced general election in Ethiopia. She has had a troubled relationship with Ethiopia’s late Prime Minister Meles Zenawi, who she still calls “a dictator,” after she published her report in which wrote the election was massively rigged. Eight years later, Ana Gomes came to Ethiopia to participate in the just concluded 26th ACP-EU parliamentary meeting. Her arrival in Addis Ababa caught many, who thought she would never be allowed to set foot in Ethiopia, by a surprise. Addis Standard’s deputy-editor-in-chief Tesfaye Ejigu met Ana Gomes during the meeting and held an exclusive interview. Excerpts:
AS - Your question to the development commissioner Andris Piebalgs was on Ethio-Djibouti road project funded by the EU. The commissioner replied EU no longer funds road projects in Ethiopia because construction work is given to companies without auction or given to friendly companies. What happened to the Ethio-Djibouti road project at the end?
Ana- Gomes - I don’t know if it was the auction. I raised the issue because some very concerned European friends told me about that because there is a lot of money from the European taxpayers which was supposed to be directed to development that was diverted. I only talked about the road. But I just confirmed with the EU commission representative that it’s indeed two contracts; one, a railway between Addis Ababa and Djibouti; the EU funding was around 45 million Euros, and two, 50 water tunnels project, by the same company worth 20 million Euros. The company was an Italian company called CONSTAT. That company adds Ethiopian Contractors/subcontractors. Obviously it was chosen by the ministry of finance with EU agreement. It’s a project that has gone very wrong because nothing has been achieved, and the money has been deviated.  EU has started investigation, arbitration is going on; it also involved your government.  And support has been cancelled. They are apparently trying to recover the money from the company. But the money has gone, so the investigation goes on. I was promised for the details by the European commission. It doesn’t mention road. It’s a bit weird however that the EU development commissioner mentioned road construction. And the EU signing new agreement to fund road projects in Ethiopia is contradictory. I think it’s important to clarify all these contradictions for the sake of taxpayers in Europe and also for the Ethiopian people. I am heartened by the fact that PM Hailemariam [Desalegn] has started taking measures even against the high officials who are involved in corruption. So I have to find out. In fighting corruption the main element is transparency. So this element has to be put out for the people to know. There are some things to be checked.qoute2
AS - EU funded hydropower project-Gilgel gibe 3 was given without auction to Salini Construction, an Italian company. A few months after it went operational part of it caved in and was closed. The EU criticized openly the handing out of the construction without auction. But it didn’t decide not to fund hydropower projects.
Ana Gomes - I am very interested to learn about that. I need to note down that information. I will find out about it and ask the EU.  I am glad you asked this. I have not been able to follow in detail all this development processes because I was not in the EU development committee.
AS - ACP-EU joint parliamentary assembly has democratic agenda. The speaker of the house of people’s representative of Ethiopia Abadula Gemeda said, “we have achieved a lot in building democracy, peace and good governance.” Do you buy that? Do you think a lot has been achieve?  
Ana Gomes - No! In many respect I see a lot of the old ways. Meles was an expert in using jargons such as good governance, the rule of law, democracy, sustainable development, but in practice doing just the opposite. It was a smart leadership which uses politically correct languages for Europeans and Americans consumption. But the practice was really oppressive. What I saw during Meles Zenawi was a dictatorship. I have lived in dictatorship in my own country. I believe this persists in the mind set of many authorities.
But at the same time, I realize there is indeed some opening, some realization [that] Ethiopia can’t continue this way.  Ethiopia needs change. Even some of the people who have that politically correct speech that everything has been achieved in Ethiopia in public, in private conversation with me they acknowledged that Ethiopia needs change, and that it is the time to really promote important, drastic changes. In that sense I welcome the move that the PM Hailemariam has initiated the prosecution of high officials, even a minister charged with corruption. I hope this will be the first step in the right direction. At the debate we were discussing the independence of the judiciary.  I used the debate to say that Judicial Independence doesn’t exist in Ethiopia, although it’s stated. I recalled the judges who flee the country in 2005 because they refuse to tamper with the conclusion on the inquiry about the massacre in 2005. They were pressed by the [late] PM and the government to do that. These were very courageous people who put all their lives and their families [at risk].  I also highlighted that trials of all political prisoners but in particular journalists Eskinder Nega, Wubeshet Taye, Riyot Alemu and others like DebebeEshetu; [political] leaders Andualem Arage e.t.c. were not fair; all the people [including] Europeans who were able to be present at some of these trials said they [the prosecutors] never produced any significant evidence against them and indeed the trials were not fair.  So I hope I have made this appeal today here.
AS - But they faced terrorism charges…?
These terrorist charges are not credible, so I appeal for their liberation in the spirit of openness. You have now a sort of dual register. In public it said one thing in private it acknowledges that Ethiopia must change. Or Ethiopia needs support to change. In that context, indeed bold decisions should be taken to liberate these people, because some of these people are icons of the younger generation. Very educated, qualified generation which Ethiopia needs to develop itself. I receive a mail, a standard letter everyday from an Ethiopian who manages to flee the country and who is somewhere in Kenya, Uganda ….Nigeria asking me to write a letter to the UNHCR saying they need political asylum. So I know Ethiopia looses the best, most qualified generation not only because of lack of jobs but because there is politically closed environment with which these young qualified people cannot live. I know Ethiopia faces serious terrorist threat as we all do, Ethiopia in particular because of the neighborhood and the tension that has been built up by Meles Zenawi between Muslims and Christians inside Ethiopia which was not an issue in 2005 but in the meantime became a big source of concern.  If the government continues the old ways repressing this bright, younger people who are now connected to the world in a way the regime cannot control them via the twitter, and facebook, and so on. Obviously many of these young people will be driven into the hands of radicals and extremists. Even to be recruited by terrorists.  It is what we see happening in other countries in the region. So, it is very important to open up democratically for the security of the country.
AS - in 2015 Ethiopia will hold a general election. Do you think it will be democratic, free and fair given the situation now?
qoute1 Ana Gomes - I don’t know, but I hope it could be good. Meles died, he was the source of the repression;his own supporting group are divided. They are fighting with each other. There is indeed an opportunity to see Ethiopia change progressively, peacefully. Nobody wants to see Ethiopia destabilized. But to create the conditions for the election to be held democratically it requires the opposition to be allowed to operate, which is not the case in the moment. In the moment you have only one member of the opposition [in the parliament]. I recall in 2005 at least there were some results that were not disputed. And these are the results of Addis Ababa where all the 23 seats went in a shocking landslide victory to the opposition. Well, where are these people? In exile.
They say the opposition is weak, of course it is weak. “it is weak, it is fragmented, it is not loyal…” are the same kind of things that I used to hear in 2005 from Meles Zenawi. But any opposition in that condition in any country would be weak. In my own country do you think the opposition in the days of the dictator was stronger? No!  Most of it was underground. In order to have the conditions to operate I believe it is important to allow the opposition to operate, not just those inside the country but also those forced into exile. They need guarantee to operate. There is no media freedom, only an opening seen. I read the Ethiopian herald and it’s all the same thing only better because PM Meles Zenawi is not writing now. There is no condition for NGOs or civil societies to operate. I believe EU will not accept to come back and observe election and give its temp of credibility unless basic elements are met; such as liberating political prisoners or allowing the judiciary to operate independently.
AS - “Europe could definitely make the difference for democracy in Ethiopia. Instead, current European leaders are choosing to fail it. In doing so they are not just failing Ethiopians. They are also failing Europe.” This is taken from a letter you wrote to AP. By this do you mean Europeans aren’t trustworthy? They don’t like democracy to thrive in Ethiopia?
Ana Gomes - No! European citizens, European taxpayers, European Parliamentarians  care about Ethiopia, democracy, development in  Ethiopia, the efficiency of development assistance but the problem is they don’t know what happens in Ethiopia. They are fooled by the leaders; leaders in the council of ministers and in the European commission. And also the development industry prevailing should continue without trouble. That is their vested interest. The tragedy is many people don’t understand what is happening in Ethiopia.  I was very happy that finally EU human rights sub-committee came last July. They are very serious, knowledgeable colleagues of mine. It was eye opener. They asked to visit Kalite Prison and the PM allowed them but was rudely treated by the Prison administration. That is an eye opener.
AS - EU and Ethiopia are development partners today as well as then. When you were not on good terms with the regime in 2005 did EU stand by your side?
Ana Gomes - The then commissioner in charge of foreign affairs and human rights stood by me always. She was not from my party but very serious. I appreciated. But the then development commissioner Mr. Louis Michel didn’t support me. Some people from his services in Brussels even tried to rewrite my report to water it down. I didn’t accept that. Several moments, my views were attacked. They supported the campaign against me which the government of MelesZ enawi spread. But Meles has gone! This is a new timing. I am pleased I was granted visa without preconditions.
AS - You were lobbying with the EU member states accusing the Ethiopian government of violating human rights. Do you think the situation has improved now?
 Ana Gomes - I know it was not easy for the new PM to assert his role as PM.  I know there was a lot of internal fighting within the power. He is not a Tigrian.  I value the visa I was given. I value the move against corruption. I sense some change.
AS - I saw you with the speaker of the house of people’s representative, AbadulaGemeda and Ambassador Teshome Toga. You had lunch with them may be. But you were not on good terms with them?
Ana Gomes - There was nothing personal; even with Meles Zenawi.  Even these professionals who were instrumental, I have nothing personal against them.  I don’t pretend to know well this country.  Ethiopian people really marveled me. Ethiopia has a great resonance in my country.  My ancestors 500 years ago were looking for Prester John.  However, Ethiopia has a magical resonance in my childhood. Ethiopia is special. Ethiopia is a civilization; not any country. It is a civilization.
 AS – You said “the EU is not only misusing European taxpayer’s money, but supporting an illegitimate status-quo, letting down all those who fight for justice and democracy and increasing the potential for conflict in Ethiopia and Africa.” But conflict in Ethiopia rises sometimes due to terrorist threats. Do you agree?
Ana Gomes - Not only the Muslim-Christian conflict Meles Zenawi fueled by trying to interfere in the Muslim community leadership but also in Ogaden.  All the report we receive in the EU are disastrous, horrendous and I am very sorry to see the Ethiopian army involved in all of thatTerrorism is an excuse; subversion was in the days of the dictatorship in my country.  Now the buzzword is terrorism. It serves to excuse, and to erase any rules, principles and values. I don’t accept it. I am very conscience of the terrorist threat. It is strong democratic societies who are better empowered to fight terrorism, not those with high level of poverty, unemployment and of internal conflict. That is the situation in Ethiopia now. I hope this can be sorted out.
AS - “Western leaders resist speaking up against Zenawi’s regime by invoking stability interests. Besides attempting to depict Ethiopia as a success story of development assistance, EU and the US like to portray their ‘aid darling’ as a partner in the fight against terrorism and a crucial actor for stability in the horn Africa,” do you still believe in this statement of yours?
Ana Gomes - I hope Ethiopian people will be able to make the distinction between this bankrupt leadership in Europe which brought us into the big economic crises which is also political crises and the people of Europe who really are serious about democracy, human rights and the rule of law.
 AS - Do you think the EU and the USA still see the regime as a partner and a crucial actor for stability or do you see any change in their position?
Ana Gomes -  I think they do. But on the other hand they also appreciate the limits of that partnership in the sense that they understand the big tensions that have been developing in Ethiopia and in the region; namely lack of effectiveness in fighting terrorism and deterring terrorism to infiltrate. I think the Americans understand it better.
Within the Obama administration there is a realization that you cannot have security without real development, not fake development and numbers but without democracy. The Americans were much more effective in getting people out of jail. The American’s pressure had political prisoners freed; opposition leaders and Birtukan Medeksa and others. They realized these three elements are linked, although they have their own flout in fighting terrorism. I was told the new American ambassador to Ethiopia is outspoken about human rights. I hope it translates into a more principled approach on the part of the Obama administration.
AS – a lot of Ethiopians respect you. They gave you an Ethiopian name. Ethiopians like honesty. Are you aware of your name? Do you know what it means?
Ana Gomes - Yes! I am aware of it. Ethiopian friends told me about it. They told me “Ana Gobeze” I am flattered, I don’t deserve it. They told me that ‘Gobez’ means brave. I have been happy meeting Ethiopian community in different countries and also received fantastic ‘Kaba’ as a gift from Ethiopians inSweden.

የ“ሎሚ” መፅሄት ዋና አዘጋጅ ክስ ቀረበበት



ሎሚበትግራይ ክልል ፖሊስ ክስ የቀረበበት የ“ሎሚ” መፅሄት ዋና አዘጋጅ ሰናይ አባተ የክሱ መነሻ በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም “የትግራይ እስር ቤትና ጓንታናሞ” በሚል ርዕስ የታተመ የአቶ አስገደ ገብረስላሴ ፅሁፍ እንደሆነ ገለፀ። በትግራይ ክልል ሁለት ልጆቻቸው መታሰራቸውን በመጥቀስ አቶ አስገደ ባቀረቡት ጽሑፍ፣ እስር ቤቱ በተራራ የተከበበ አስጨናቂ ሸለቆ በማተት አሸባሪዎች ከሚታሰሩበት፣ ከጓንታናም ጋር አመሳስለውታል፡፡ የትግራይ ፖሊስ በበኩሉ፣ የአቶ አሰገደ ጽሑፍ የእስረኞች አያያዛችንን ለማጠልሸት እና የፖሊስን ተአማኒነት ጥርጣሬ ላይ ለመጣል ያለመ ነው ሲል ክስ ማቅረቡን የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ተናግሯል፡፡ ሐሙስ ረፋድ ላይ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተገኝቶ ቃሉን የሰጠው ዋና አዘጋጁ፤ “ፅሁፉ በሎሚ መፅሄት ከመታተሙ በፊት በኢትዮ ምህዳር ጋዜጣም ላይ ተስተናግዷል” ብሏል፡፡ ታተመ የመጣ ጽሑፍ በህግ ሊያስጠይቅ የሚችለው ከስድስት ወር ላልበለጠ ጊዜ እንደሆነ በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ላይ የተገለፀ ሲሆን፤ ፅሁፉ ከተስተናገደ ከሰባት ወራት በኋላ ክስ የቀረበበት ምክንያት አልገባኝም ብሏል – ሲሳይ አባተ፡፡ “አቶ አሰገደ ትግራይ ውስጥ እየበጠበጠ ያለ ሰው ነው፤ ፅሁፉን እንዴት አግኝታችሁ አስተናገዳችሁ” በሚል በመርማሪዎች ጥያቄ እንደቀረበበት የገለፀው ዋና አዘጋጁ ሲሳይ አባተ፤ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች ላይ በመፃፍ የሚታወቁት አቶ አሰገደ ፅሁፉን ልከውልን እንዳስተናገድን ተናግሬያለሁ ብሏል፡፡
ናፍቆት ዮሴፍ

ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር በተያያዘ በሳውድ አረቢያ ከፍተኛ የሆነ አደጋ ማንዣበቡን ኢትዮጵያውያን ተናገሩ


በሳውድ አረቢያ የሚታየው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ዜጎች። ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያን በእስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀናቸውን ይጠባባቃሉ። የኢትዮጵያ መንግስት በመቶ ሺ Africansየሚቆጠረውን ስደተኛ ለማስተናገድ የመደበው የሰው ሀይል 40 ብቻ ነው። የሳውድ አረቢያ መንግስት ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ምድር ተጠራርገው እንዲወጡ እየቀሰቀሰ ነው። ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ አደጋ ሊፈጠር ይችላል ብሏል  አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ጋዜጠኛ።
በዛሬው እለት በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተነው የኤስ ኤም ኤስ መልዕክት  ህጋዊ ለተባሉትም ሆነ ህገወጥ ለሚባሉት ኢትዮጵያውያን የማስጠንቀቂያ ደወል ነው ይላሉ እኝህ ጋዜጠኛ።
በሞባይል ስልኮች የተበተነው ኤስ ኤም ኤስ ኢትዮጵያውያንን ቀጥራችሁ የምታሰሩ እንዲሁም መኖሪያ ቤት ያከራያችሁ ሁሉ በአስቸኳይ እንድታስወጡ፣ ይህን ባታደርጉ ግን 100 ሺ ረያል ትከፍላለችሁ የሚል እንደሆነ ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል። ይህን መልእክት ተከትሎ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከተከራዩበት ቤት ተባረዋል። 9 ኢትዮጵያውያንን ወደ አስጠጋው ኢትዮጵያዊ በመደወል መታሰቢያ ቀጸላ አነጋግራቸዋለች። እርሱ እንደሚለው መልክቱ መተላለፉን ተከትሎ ጓደኞቹ ከቤታቸው እንዲወጡ ተደርጎ በእርሱ ቤት ተጠልለዋል::
ከቤታቸው ከተባረሩት መካከል አንዱ ከ8 ወራት በፊት አባቱ ቤታቸውን ሸጠው ፣ በኪራይ ቤት እየኖሩ በህጋዊ መንገድ እንደላኩት ይናገራል። አሁን ቤትክን ለቀህ ውጣ ተብሎ ህይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል::
የሳውዲ መንግስት በኦፊሴል እንዲህ አይነት መልክት ያስተላልፍ እንደሆነ የጠየቅነው ጋዜጠኛ፣ መንግስት በቀጥታ እንዲህ አያደርግም ነገር ግን እርሱ ባሰማራቸው ሰዎች አማካኝነት መልክቶችን እንደሚሰድ ይታወቃል ብሎአል።
የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ የዲፕሎማሲ ዘመቻ በማድረግ በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ህይወት መታደግ ሲችል በቀን ይህን ያክል ሰው አስመጣሁ በማለት ፕሮፓጋንዳ ይነዛል የሚለው ጋዜጠኛው፣ በሳውዲ የቀረው ኢትዮጵያዊ ወደ አገር ቤት የተመለሰውን በብዙ እጥፍ ይበልጣል ሲል በአገሪቱ ያለውን እውነታ አስረድቷል።
በሌላ በኩል ከሳውድ አረቢያ ወደ የመን የገቡ 3 ሺ ያክል ኢትዮጵያውያን በምግብ እጥረት ተጎሳቁለው እንደሚገኙ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሀይማኖት ጎብኝቷቸዋል።

fredag 29. november 2013



ESAT NEWS 28/11/2013
ESAT NEWS 29/11/2013
ESAT NEWS 27/11/2013

ተዋርደን አንቀርም!!!

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡

ወቅታዊ ችግሮቻችን የራሳችን መንግሥት ባለቤቶች እንድንሆን 

ይበልጥ ሊያበረቱን ይገባል!


በወያኔ አረመኔያዊ አገዛዝ ሳቢያ ከሀገራቸውና ከትውልድ ቀያቸው ተፈናቅለው በዐረቡ ዓለም በተለይም በሳዑዲ ዐረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ ሰሞኑን እየደረሰ የሚገኘውን ዘግናኝ ሰቆቃና ግድያ በመሪር ስሜትና በንቃት እየተከታልን ነው። አበው “ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳው አይቀበለውም” እንዲሉ እነዚህ ወገኖቻችን በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ‹የሀገራቸው መንግሥት ነው› የሚባልለት የወያኔው መንግሥት እንኳንስ በባዕድ ሀገር በሚገዛው ሀገርም ውስጥ የሚያካሂደውን የመብት ገፈፋና ሕዝቤ በሚለው ዜጋ ላይ በዘር እየከፋፈለ የሚያራምደውን የግፍ አገዛዝ ዐረቦቹም ሆኑ ቀሪው ዓለም ያውቁታል። በመሆኑም ለነዚህ ምሥኪን ዜጎች የሚጮኽላቸውም ሆነ ለመብታቸው መከበር የሚቆረቆርላቸው አንድም መንግሥታዊ አካል እንደሌለ ከበፊት የተገነዘቡት እውነታ ነው። በወገኖቻችን ላይ ይህን ሁሉ ሰማይና ምድር የማይችሉት የግፍ ቁልል እነዚህ የዐረብ መንግሥታት የፀጥታ ኃይሎች ሲከምሩባቸው ማንም ዝምባቸውን እሽ የሚል ወይም ጠንከር ባሉ ቃላት እንኳን ተቃውሞ የሚያቀርብ አካል እንደማይር ያውቃሉ። ለዚህም ነው ታላላቅ የሚዲያ አውታሮች ሳይቀሩ ሀገሪቷንና ሕዝን በመናቅ በዝምታቸው መግፋትን የወደዱት። ይህ ነገር ከሃይማኖትም ይሁን ከቀለም፣ ከዘርና ከፖለቲካዊ እሳቤዎች አኳያ የሰው ልጅ ተፈጥሮን ባሕርይና የሀገራትንና የመንግሥታትን ተጻራሪ ድርብ አቋሞችን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። “ሰው ለሰው የሚጨነቀው፣ ምን ዓይነት ሰው ሲጎዳ ወይም ምን ዓይነት ሕዝብና የትኛው ሀገር ችግር ላይ ሲወድቅ/ሲወድቁ ይሆን?” በሚል ከፍተኛ ፍልስፍና ውስጥ የሚያስባ ልዩ አጋጣሚ ፈጥሯል። በእውኑ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሕዝብ በበለፀጉ ሀገሮች የአንድ ንጉሥ-ንግሥት ንብረት ከሆነች ውሻ ያንሳሉን? ንግሥት ኤልሣቤጥ የሚወዷት የቤት ድመት ወይም የንጉሥ አብደላ የቤተ መንግሥት ውሻ ቢሞቱ ሲኤንኤንንና ቢቢሲን የመሳሰሉ ላለው የሚያሽቃብጡ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት የመክፈቻ ዜናቸው እንደሚያደርጓቸው አይጠረጠርም። ወትሮም ብሂሉ “ላለው ይጨመርለታል” ነውና። እንደዚህ ያለው አካሄድ በውነቱ ቅስምን የሚሰብርና ከ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰለጠነ የሚባል ማኅበረሰብ የሚጠበቅ አልነበረም።