fredag 20. mars 2015

የሀሃገሪቱን ሃብት የወያኔ ባለስልጣናት ለሊቱን የጉምሩክ መጋዘኖችን ሲዘርፉ አደሩ!

ሳተናው ዜና
0
  • 2824
    Share
10395167_10203594184165064_8271715634568534826_nበሃገሪቱ አንጡረ ሃብት ላይ ከፍተኛ ዘረፋ እና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጭቆና በማድረግ ላይ የሚገኙት የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት በጄኔራሎች እና በደህንነት ባለስልጣናት እየተመሩ ለሊቱት ከጉምሩክ መጋዘኖች በውርስ የገቡ እቃዎችን ሲጭኑ ያደሩ መሆኑን ምንጮች ከአዲስ አበባ ገልጸዋል::
ለሊቱን በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የጉምሩክ መጋዘኖች የተወረሱ የመኪና መለዋወጫዎች የኤሌክትሮኒስ እቃዎች የሞባይል ቀፎዎች ውድ ጌጣጌጦች የቤት እቃዎች የመሳሰሉት በባለተሳቢ መኪናዎች አስጭነው መውሰዳቸው ሲታውቅ እቃዎቹ በሃገሪት በተለያየ አከባቢ ተበትነው እንደሚሸጡ ምንጮቹ ገልጸው ለሊቱ የጄነራል ሳሞራ የኑስ የሜ/ጄነራል ተክለብርሃን እና የአርከበ እቁባይ መኪኖች እና ጠባቂዎቻቸው እና ተላላኪዎቻቸው በየመጋዘኖቹ ሲዘዋወሩ እንደነበር እና ለዚህ ዘረፋ ተሳታፊዎቹ እነማን እንደሆኑ በግልጽ ያሳያል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል::
የወያኔ ባለስልጣናት ሕዝብን እየጨቆኑ እየዘረፉ እስከመቼ እንደሚቀጥሉ የሚያሳስብ ጉዳይ መሆንን አውቀን ህዝብን እና ሃገርን ከዘረፋ እና ከጭቆና ለማዳን ከለውጥ ሃዮች ጎን በመቆም በሃገር ውስጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በአስተባበር እና ሕዝብን በመቀሰቀስ ከአስከፊው ስርአት ነጻ ለመውጣት በጋራ መንቀሳቀስ አለብን:: ነጻነታችንን ማራጋገጥ የምንችለው እኛው ታግለን መሆኑን ማውቅ ያለብን ወስኝ ወቅት ላይ ስለሆንን በአንድነት በመቆም ይህንን የሌቦች መንግስት ስርአተ ቀብር እናጣድፈው ዘንድ ጠንክረን መስራት አለብን::

እናቶችን የሚያስለቅስ አገዛዝ – የፍርድ ድቤት ዉሎ

 

0
  • 662
    Share
የካትት 10/2007 ዓም የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀበት የነዘመነ ምህረት ችሎት፣ በቀጠሮው መሠረት፣ ዛሬ መጋቢት 10/2007 ዓም ተሰይሟ።
1797602_350367271835285_7444822617832808936_nዘመነ ምህረት፣ መለሰ መንገሻና ሌሎች ወደ 25 የሚጠጉ ወጣቶች በማእከላዊ ፓሊሶች ታጅበው 8:ሰአት 20 አካባቢ ፍርድ ቤት ግቢ ገቡ። እንደተለመደው በርቀት እጃቻችንን በማውለብለብ ሰላም አልናቸው። እነሱም ባልታሰረው እጃቸው አፀፋውን መለሱልን።
ዘመነ ምህረት ብዙም አልተጎሳቆለም። መለሰ መንገሻ ግን በጣም ከስቷል። ሰውነቱ ቢጫ ሆኗል። እንደዛም ሆኖ ፈገግታ ግን አልተለያቸው። ችሎት ከመግባታቸው በፊት የተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ላይ ሆነው፣ በምልክት ለመነጋገር ሞክረን ለመግባባት ችለን ነበር። ነገር ግን ፓሊሶች ከኛ ጋር የሚያደርጉት የምልክት መግባባት አይተው፣ ፊታቸውን አዙረው አስቀመጧቸው ። ተስፋ ሳንቆርጥ ሞከርን። አልተሳካም።
የችሎት ሁኔታ እንደሚታወቀው በዝግ የታየ በመሆኑ የነበረውን ሁኔታ ማወቅ አይቻልም። ዘመነና መለሰ መንገሻ ችሎት የገቡት ተለያይተው ነው። ከዚህ መረዳት የሚቻለው የተከሰሱበት መዝገብ ይለያያል ማለት ነው ። ሁለቱም ችሎት ሲገቡ ሌሎች ወጣቶች አብረዋቸው ገብተዋል።
የዛሬው የችሎት ሁኔታ ተጨማሪ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ፓሊስ ጠይቆ ለመጋቢት 08/7007 ዓም ተቀጥሯል።
አንድነት ዘመነ ምህረት፣ የዘመነ ምህረት የበኩር ልጅ፣ በፍርድ ቤት አልተገኘም። የሕጻን አንድነትን ቦታ ተክተው፣ ከሰሜን ጎንደር ተጉዘው የመጡት፣ የቆራጡ ታጋይ ዘመነ ምህረት እናት ነበሩ። እኚህ እናት ታማሚ ናቸው። የወለደ አንጀታቸው አልችል ብሏቸው ህመማቸውን ችለው፣ ከሰሜን ጎንደር፣ ከ700 ኪሎሜትር በላይ ተጉዘው፣ «ልጄ በህይወት መኖሩን ካላየሁ አላምንም» ብለው፣ አራዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ተገኝተዋል። በጣም ያሳዝናሉ።
የመጡበትን ምክንያት የልጃቸውን በህይወት መኖር አለመኖር ለማረጋገጥ ነበር። በካቴና ታስሮም ቢሆን አይተዋል። በውስጣቸው ምን እንደተሰማቸው ባላውቅም። ጥልቅ የሆነ ሀሳብ ገብቷቸዋል። ለሰው ከመናገር ዝምታን ። ከኚህ የጀግና እናት ጋር ትንሽ ለመጨዋወት ሞክረን ነበር ። እንባቸው እየቀደማቸው ማውራት አልቻልንም። በመጦሪያቸው ጊዜ መንከራተት በጣም ያማል። እስኪ የኝህ እናት ፀሎት ተሳክቶ ዘመነ ተፈቶ ከመንከራተት ያድናቸው ዘንድ እንፀልይላቸው ።
 ሳተናው ዜና

(ለገሰ ወልደሃና)

tirsdag 17. mars 2015

ልዩነታችን ጌጣችን፤ አንድነታችን ህልውናችን ነው


ልዩነታችን ጌጣችን፤ አንድነታችን ህልውናችን ነው

ልዩነታችን ጌጣችን፤ አንድነታችን ህልውናችን ነው

March 17, 2015
pg7-logo
ኢትዮጵያ ስንል ብዙ የተለያዩ ዘውጎች፤ ብዙ የተለያዩ ቋነወቋዎችና ሀይማኖቶች በአንድነት ይዛና አስተሳስራ ብዙ ፈተ ናዎችን በማለፍ ለረጅም ዘመናት ህልውናዋን ጠብቃ የቆየች ሀገር መሆንዋ መታወቂያዋ ሀገር ማለት ነው። እንዳ ሳለ ፈችው ረጅም ዘመናት ሁሉ እንደየዘመኑ በህልውናዋ ላይ ይቃጣ የነበረውን ጥቃት እነዚያ በዘውጎች፤ በቋነወቋዎችና ሀይ ማኖቶች የተንቆጠቆጡት ልጆችዋ በአንድነት በመሰለፍ ብሎም ድል በመምታት ህልውናዋን አስጠብቀው መዝለቃቸው የነጻነት ሀገር የመሆን መለያዋ ምክንያቶች መሆናቸውንም የሚያሳይ ነው።
ይህ ልዩነታችንን ጌጡ አድርጎ ያስተሳሰረን ኢትዮጵያዊነት በነፃነት የዘለቀ ህዝብ ከማድረግ አልፎ በአንድ ወቅት የስልጣኔ ምንጭና የአለማችን ሀያል ህዝብ ከመሆን ጫፍ አድርሶን እንደነበር አይዘነጋም። በዚያው ልክ ይህ በልዩነታችን ላይ የተገነባ አንድነታችን ሲላላ ህልውናችን ከገደል አፋፍ ላይ የደረሰበት ዘመንም በታሪካችን ውስጥ መታየቱ አልቀረም። “ዘመነ-መሳፍንት” በመባል የሚታወቀው ጥቁር የታሪካችን ክፍል አንዱ ተጠቃሽ ሲሆን ሌላው ዛሬ የምንገኝበት የወያኔ ዘረኛ ዘመን ነው። ትናንት በዘመነ መሳፍንት ህልውናችን አደጋ ላይ ወድቆ ነበር፤ ዛሬም በወያኔ ዘረኞች ዘመን ህልውናችን ከከፋ አደጋ ላይ እንዲገኝ ተደርጓል። በአጭሩ ልዩነታችን ጌጣችን አንድነታችን ደግሞ የህልውናችን ማስጠበቂያ ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን መገንዘብ ለማናም አያዳግትም።
ሌላው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በታሪካችን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ በህልውናችው ላይ የከፋ አደጋ ያንዣበበት ወቅት ላይ መገኘታቸው ከማንም የተሰወረ አይደለም። ዘመነ መሳፍንት ትናንት ቋንቋ ዘውግና ሀይማኖት ሳይለይ በእያንዳዱ ኢትዮጵያዊ ህይወት ላይ አስከትሎት የነበረውን ችግርና በሀገሪቱም ከአዘቅት የከተተ ከመሆኑም በላይ ይኸው እስከዛሬ ድረስ ውደ ቀድሞ ታላቅነቷ ለመመለስ ከባድ መሰናክል ተክሎ ማለፉን ከትናንት ታሪካችን መረዳት እየተቻለ ዛሬ በእኛ ዘመን ዳግም ከትናንቱ የከፋ ጥልቅ አዘቅት ውስጥእንድንፈቅ በዘረኞች እየተገፋን መሆኑንና ሊያስከትል የሚችለውንም ውጤት ለመረዳት የተለየ እውቀት አይፈልግም። ዛሬ ይህ ልዩነትን እያጎሉና ቂም በቀልን እየዘሩ መጓዛ የጥቂቶች ፍላጎት መሆኑ ባይካድም ከዚህ ቀደም ያስከተለውንና ዛሬም እየታየ ያለውን አደጋ ተገንዝቦ ከወዲሁ መከላከል የእያንዳዳችን ሀላፊነት ሊሆን ይገባል።
ጥቂቶች የህዝብ አሳቢ በመምሰል የሚረጩት የልዩነት መርዝ በሌሎች ሀገራት ላይ ያስከተለውን ፈተናም እንዲሁ ቆ ም ብሎ መፈተሽና ውጤቱንም መመዘን የፈሰሰ ውሀን አፋሽ ከመሆን ማዳኑን መጠራጠር የለብንም። የሶቭየት ህብረት መ ፍረስ፤ የዩጎዝላቪያ እርስ በርስ መባላት፤ የሶማልያ መቋጫ ያጣ ትርምስ ……. ወዘተ ንፁሀንን በገፍ የበላና ዜጎችን ለኢኮኖሚ ድ ቀት የዳረገ፤ በገፍ ስደትን ያስከተለ፤ የጦርነቶቹ መዘዝ ከልጅ ልጅ የማይታረቅ ቂም እያስቋጠረ መገኘቱ ሲታይ ዛሬ በእ ኛም ሀገር ጥቂት የመገንጠል አባዜ የተጠናወታቸው ይዘውን ሊጓዙ የሚፈልጉበትን መንገድ የት ሊያደርሰን እንደሚችል ከራ ሳችንም ያለፈ ታሪክ ሆነ በአለማችን ላይ የታዩ ክስተቶች ውጤት የሆነውን ትርምስና ሽብር በመመልከት ልንማርበትና ከወዲሁ አንድነታችንን በማጠናከር ለመከላከል መስራት ግድ ይለናል።
ከላይ እንደ ምሳሌ የተጠቀሱት ሀገራት በመበታተን ያተረፉተረ ሽብረ፤ ጦርነት፤ ስደትና ድህነት መሆኑ የታዘብነው የዘመናችን ክስተት ሲሆን ቀደም ሲል ለሁለት ተከፍላ የነበረችው ጀርመን ዳግም ከሁለትነት ወደ አንድነት መምጣቷዋ በሰጣት ሁለንተናዊ ጥንካሬ የዓለምችን ታላላቅና ሀብታም ሀገራት በኢኮኖሚ ውድቀት ሲመቱ ያለአንዳች ጭግር የፈተናውን ወቅት ያለፈች ሀገር ለመሆን መብቃትዋን ከአንድነት ሊገኝ የሚችለውን ሁለንተናዊ ጥንካሬ አጉልቶ የሚያሳይ ነው። ሌላው ከሀ ገራችን ህልውናን የማስጠበቅ ፍልሚያ ታሪኮች ውስጥ ጎላ ብሎ የሚታየው የአድዋ ጦርነትና ድል የአንድነትን ዋጋ ከፍ አድርጎ የሚያሳይ አኩሪ ታሪክ ነው። በዘመናዊ የጦር መሳሪያ ተማምኖ የመጣውን ወራሪ የኢጣልያ ጦር በተመጣጣኝ የጦር መሳሪበ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ተማምኖ የመጣውን ወራሪ የኢጣልያ ጦር በተመጣጣኝ የጦር መሳሪያና የሰለጠነ ሰራዊት ሳይሆ ን ቋንቋ፤ ዘውግና ሀይማኖት ሳይለያቸው ሁሉም በአንድነት ለሀገራቸው ህልውናና ለነፃነታቸው በአንድነት በመቆማቸው የተ ገኘ ድል መሆኑም መዘንጋት የለበትም።
ኢትዮጵያችን ደሀ ናት? አዎ ደሀ ናት። ህዝቧም ለዘመናት አንባገነን ስርአቶች እየተፈራረቁበት ህይወቱ የስቃይና የመከራ ሆኖ ቆይቷል? አዎ ቆይቷል። ሀገራችንን ከድህነትና ከዃላ ቀርነት፤ ህዝቧንም ከስቃይና ከመከራ ህይወት አውጥቶ የተሻለ ሀገር፤ ለመፍጠር ዛሬ የወያኔ ዘረኛ ቡድን የሚያራምደው የመንደር ፖለቲካ እውን መፈትሄ ነውን? ብለን ስንጠይቅ ያለፉት 23 የወያኔ የስልጣን ዘመናት እውነቱን ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ። በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ ህዝብ በጅምላ ስደት፤ ለቁጥር በሚታክት ሁኔታከመኖሪያ ቀዬ መፈናቀል፤ እስር ቤት በእስር ቤተረ መገንባት፤ እናትና ልጅ ተፈራርተው መመካከር ያልቻሉበት ዘመን፤ ድህነት ከሚባለው ደረጃ ተወርዶ ጭራሽ የሆቴል ትርፍራፊ በጉርሻ የሚሸጥበት ዘግናኝ ወቅት ላይ ለመገኘት ምክኒያት ከመሆኑም በላይ ሀገር አለኝ ብሎ መኩራት እንኳ ከማይቻልበት ህልውናችን ከከፋ አደጋ ላይ የሚገኝበት ወቅት ሆኖ እናገኘዋለን።
ዜጎችን ነቋንቋ በዘውግና በሀይማኖት ከፋፍሎ ለመግዛት የሚያራምደው በታኝ የጥፋት ፖለቲካ ሌላው ቢቀር ዛሬ በቀን ሶስት ጊዜ በልቶ የማደር ሰዋዊ መብት እንኳ ማስከበር ከማይቻልበት ሁኔታ ላይ መደረሱ ከእያንዳዱ ኢትዮጵያዊ የተሰወረ አይደለም። በአንባገነኖች የተጫነበትን የአገዛዝ ቀንበር አስወግዶ የነፃነት አየር የሚተነፈስበት፤ ፍትህ የሰፈነበትና መብቶች የተከበሩበት ሀገር ለመፍጠር በተከፊለ የህዝብ ልጆች የህይወት ዋጋ ለስልጣን የበቃው ወያኔ በማር በተለወሰ መርዘኛ የዘር ፖለቲካው ሳቢያ የተገኘው ውጤት የእለት ጉርስን እስከማጣት የደረሰ ሆኗል ማለት ነው።
በአጭሩ ዛሬ ከ23 አመታት በዃላ እንደ ትናንቱ ሁሉ ይህን ርእሰ-ጉዳይ ማንሳታችን ያለ ምክንያት አይደለም። ይህ በለዩነታችን መካከል ለመገንባት ደፋ ቀና የሚባልለት የልዩነት አጥር እስካሁን የተፈለገውን ያህል ባይሳካም በጠንካራው አንድነታችን ላይ ያጠላው ጥላ ለምን አይነት አሰቃቂ ህይወት የዳረገን መሆኑና ጥያቄዎቻችን ለሆኑት ፍትህ፤ እኩልነትና ነፃነት ምላሽ ከማስገኘት ይልቅ ይባስ ለከፋ አፈናና አገዛዝ የዳረገን መሆኑን ተገንዝበን ቀኑ ሳይመሽ ከወዲሁ ለመፍትሄው በጋራ መስራትብቸኛ አማራጭ መሆኑን ሁሉም እንዲገነዘበው ነው።
3000 ዘመን ያለ ፈተና የተቆጠረ የነፃነት ዘመን አይደለም። የገጠሙን ፈተናዎች በሙሉ በልዩነቶቻችን ላይ በተገነባው ጠንካራ ኢትዮጵያዊ አንድነታችን ተጠብቆ የተገኘ እንጂ…… ዛሬም ቢሆን ዜጎች ልዩነቶቻቸውን የጥንካሬያቸው መሰረት በማድረግ በአንድነት ነፃነታቸው የተረጋገጠበት፤ መብቶቻቸው የተከበሩበት፤ ፍትህ የሰፈነበት ሀገር ለመፍጠር የተጀመረውን ሁለገብ ትግል በማጀብ ከዳር ለማድረስ ለመነሳት ያለፉት 23 አመታት ከበቂ በላይ መሆኑን አጢነን በቃ የምንልበት ወቅት ላይ እንደምንገኝ ለማሳሰብ ነው።
ትናንትም ዛሬም ነገም ልዩነቶቻችን ጌጣችን አንድነታችን ህልውናችን መሆናቸውን ተረድተን ሳይመሽ ሁላችንንም በእኩልነት የምታስተናግድ የሁላችንን ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ!!!!!
ኢትዮጵያችን ለዘላለም ትኑር!!!!

Ethiopia denies Temesghen Desalegn access to medical care in jail

Ethiopia denies Temesghen Desalegn access to medical care in jail

March 16, 2015
(CPJ) Nairobi, March 16, 2015–Authorities in Ethiopia have denied medical attention to Ethiopian journalist Temesghen Desalegn, who has been imprisoned since October, according to sources close to the journalist.
Ethiopian journalist Temesghen Desalegn
The health of Temesghen Desalegn has deteriorated in prison, but he has been denied medical care.
Temesghen Desalegn, owner of the now-defunct newsmagazine Feteh (Justice), isserving a three-year term in Ziway Prison, outside Addis Ababa, on charges of defamation, incitement, and false publication in connection with a series of opinion pieces he wrote in Feteh in 2012, according to news reports and a translation of the charge sheet that CPJ reviewed.
Sources close to Temesghen, including two who visit him in prison, told CPJ that Temesghen suffers from stomach and back pain for which he used to receive weekly medical support before he was jailed. The sources said that Temesghen has been denied medical access since he was imprisoned and that his back pain has worsened to the point that walking is difficult for him.
The African Charter on Human and People’s Rights, to which Ethiopia is a signatory, states that authorities are obligated to ensure that its citizens receive medical attention when necessary.
CPJ’s calls to the Ethiopian justice ministry in Addis Ababa, and CPJ’s calls and emails to the Ethiopian embassy in Washington, were not answered.
Earlier this year, prison authorities denied Temesghen prison visits from friends and family for more than a month, according to a public letter by Temesghen’s mother, Fanaye Irdachew. Authorities did not provide an explanation, but local journalists told CPJ they suspected Temesghen had been denied prison visits after an article he wrote from prison was published in several Ethiopia news websites. The articles detailed the mistreatment of prisoners at Ziway Prison.
Temesghen often criticized the authorities in his articles. In 2012, he wrote two articles that discussed the peaceful struggles of Ethiopian youth movements for political change, according to the charge sheet that CPJ reviewed. He also wrote two columns that criticized alleged government efforts to violently suppress student protesters and ethnic minorities reviewed.
“Temesghen Desalegn has not committed any crime. He is being punished for his criticism of the Ethiopian government,” said CPJ East Africa Representative Tom Rhodes. “We call on authorities to stop harassing Temesghen and allow him immediate access to medical care.”
Ethiopian authorities were holding at least 17 journalists in jail–more than twice the number as the year before–when CPJ conducted its annual prison census on December 1. Dozens of journalists fled Ethiopia in 2014 fearing arrest, CPJ research shows. Local journalists said they suspect authorities had cracked down on the press in order to silence critical voices ahead of May 2015 legislative elections.