onsdag 9. oktober 2013

የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ድምፅ ከየመን

የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ድምፅ ከየመን
በየመን እና በሳዑዲ አረቢያ ድንበር ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የሚገኙት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
የሳዑዲ አረቢያ የወሰን አጥሮች ንድፍ /በሰሜን ኢራቅ፤ በደቡብ የመን/የሳዑዲ አረቢያ የወሰን አጥሮች ንድፍ /በሰሜን ኢራቅ፤ በደቡብ የመን/

ሳዑዲ አረቢያ ከየመን ጋር በሚያዋስናት ድንበሯ ላይ በተለይ ከአፍሪካ የሚጎርፉ ስደተኞችና ፍልሰተኞችን ያስቆምልኛል ያለችውን አጥር አቁማለች፡፡ 1800 ኪሎሜትር ከሚሆነው የጎረቤቶቿ ወሰኖች በ75 ኪሎሜትር ላይ የቆመው ባለ ሦስት ሜትር ቁመት አጥር ተጠናቅቋል፡፡

ዛሬ ወደ ሳዑደ አረቢያ መዝለቅ እንደቀድሞ ቀላል አይደለም፡፡
የሳዑዲ-የመን ድንበር አጥርየሳዑዲ-የመን ድንበር አጥር

አደገኛው አጥር ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራና ከሌሎችም የአፍሪካ ሃገሮች ብዙ መከራ አልፈው የየመንን ምድር ከረገጡም በኋላ የሚከተላቸው ሥቃይ ከዚህ አጥር ማዶ ያለውን ሥራ የማግኘት ተስፋና ከጀርባ የተዋቸውን የመርዳት ህልማቸውን ያጨልመዋል፡፡
አደገኛው አጥርአደገኛው አጥር

የመን ውስጥ ሃያ አምስት ሺህ ስደተኞች እንዳሉ ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት - አይኦኤም የሚናገር ሲሆን በቅርቡ አራት መቶ የሚሆኑ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡
ስደተኛስደተኛ

ስደተኞቹ የሚደርሱባቸው በደሎችና ችግሮች የተደራረቡ እንደሆኑ የሚናገሩ ሲሆን በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር - ዩኤንኤችሲአር እና ሰንዐ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለችግራቸው ካለመድረሣቸውም በላይ እንደሚያንጓጥጧቸውና ሰብዕናቸውን የሚጎዱ አድራጎቶችን እንደሚፈፅሙ በማማረር ይናገራሉ፡፡
pic voa.
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

http://amharic.voanews.com/content/ethiopian-refugees-yement-10-03-13/1762631.html

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar