tirsdag 26. april 2016

ኢሳት እንወያይ ፕሮግራም!!


በኢሳት እንወያይ ፕሮግራም ላይ እኔ ቃልኪዳን ካሳሁን ከኖርዌ እና ሀና ለገሰ ከአውስትራሊያ እንዲሁም የእንወያይ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ጋዜጠኛ ደረጀ ሀብተወልድ ጋር በመሆን በሀገራችንና በህዝቦቻችን እየደረሰ ግፍና መከራ በተለይ በአሁን ወቅት በተለዩ ቦታዎች ህወሓት ሲፈፅምና እየፈፀመ ያለው ኢሰብዓዊ ድርጊት በመቃወም ተወያይተናል።

የዛሬው እንወያይ ፕሮግራም ከ10 ቀን በፊት በጋምቤላ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጭፍጨፋ እጅግ ዘግናኝ እና አሰቃቂ እንደነበር ሁላችንም የተመለከትነው ጉዳይ ነው። በውይይታችን ውስጥ ከመንግሥት የተሰጠው የሀዘን መግለጫ፣በመከላከያ ሰራዊቱ በክልሉ በተደጋጋሚ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋዎች እንዳሉ እየታወቁ በመንግስት ለነዋሪዎቹ በቂ ጥበቃ እንዳላደረገላቸው እንዴት ድንበር ያለጠባቂዎች እንዲሆን ለምን ተደረገ፣ ታፍነው ስለተወሰዱ ህፃናት እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ምን ይመስላል፣ከዚህ ጭፍጨፋ በስተጀርባ የህወሓት እጅ እንዳለበት እንዲሁም ጊዜውን ያልጠበቀ የሀዘን ቀን መታወጁ በተጨማሪ በሶሻል ሚዲያው ስለኢትዮጵያዊነት እጅግ በጣም ደስ እንደሚል እና ይህን በሶሻል ሚዲያ ላይ ያለውን አንድነት ወደ አንድ ነገር መደረስ እንዳለበት እና እነዚህና መሰል ችግሮችን በማንሳት ተወያይተናል።